Friday, March 30, 2012

የመንፈስ ቅዱስ እናትነት



በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
22/07/2004
የክርስቶስ ልብ የተባለ፤ የእግዚአብሔር አብ እስትንፋሱ እንዲሁም የፍጥረት ሁሉ አስገኚ የሆነው መንፈስ ቅዱስ ለእኛ ለተጠማቂያን ክርስቲያኖች እናታችን ነው፡፡ እርሱ የእግዚአብሔር ብቸኛ ልጁ የሆነውን አፍቃሪያችንን ክርስቶስ ኢየሱስን  ይበልጥ እንድናውቀውና እንድንረዳው እንዲሁም እርሱን አብነት አድርገ እርሱ የሞተለትን የሰውን ልጅ ለእግዚአብሔር አብ እንድንማርክና የእግዚአብሔር አብና የእግዚአብሔር ወልድ ልጆች፣ የክርስቶስ ወንድሞች(በጸጋ) በማድረግ እንድናቀርባቸው፤ በጥምቀት ካህናት፤ የክርስቶስ ወታደሮች፤ የእርሱ አባሳደሮች አድርጎ የሾመን ነው፡፡ ስንጠመቅ ለእያንዳንዳችን ራሱ በሰጠን ጸጋ እንደ እናት ሰብስቦ የጸጋውን ወተት የሚመግበን፣ በእርሱም ባገኘነው ክርስቶስን በሚመስል ተፈጥሮአችን በአእምሮም በአካልም በሞገስም ልክ እንደ እናት እቅፍ ድግፍ አድርጎ በፍቅር የሚያሳድገን እርሱ ነው፡፡