Tuesday, May 5, 2015

ወገኖቼ አንድ እውነት ልንገራችሁ



ከዲ/ን ሽመልስ መርጊያ

27/08/2007

 እውነቱም ይህ ነው፡- ደስታና እረፍት አይደለም በምድራዊ ሕይወታችን ውስጥ ይቅርና በመንፈሳዊው ምልልሳችን እንኳ ሁሌ የምናገኘው አይደለም፡፡ በምድር የምናጣጥማቸው ደስታና እረፍት መገኛቸው ከእግዚአብሔር ስጦታዎች እንጂ ከሌላ ከምንም አናገኛቸውም። ቢሆንም እነዚህ የሚታወኩበት ጊዜ ስለሚመጣ ያኔ ደስታህና እረፍትህ ለጊዜውም ቢሆን ሊወሰዱብህ ይችላሉ፡፡ እንዲህም ቢሆን ተፈጥሮውያኑ የእግዚአብሔር ስጦታዎች እየተጤኑ ካልሆኑ በቀር ከወይኒ ቤትም በላይ የከፉ የስቃይ እስር ቤት ሊሆኑብህ ይችላሉ፡፡
ስለዚህ ወገኔ በእነዚህ የእግዚአብሔር ስጦታዎች ሙሉ ለሙሉ ባይሆን እንኳ የደስታህና የእረፍትህ እርሾ ከአንተ ፈጽሞ እንዳይወሰድ ከፈለግህ አስቀድመህ ይሉንታን ከራስህ አርቅ ፡፡ ይሉንታ የደስታንና የእረፍትን እርሾ ፈጽሞ ከሰውነትህ የሚያስወግድና በምትኩ የማይጠፋ የቁጭት ፍም አኑሮ የሚያልፍ ነው፡፡ ስለዚህ ወዳጄ ሕሊናህ የሚልህን ስማው ፤ ሕሊና የአንተን ደስታና እረፍት ጠንቅቆ የሚያውቅና የቁጭት ፍምን ከአንተ የሚያርቅ መለኪያህ ነው፡፡
 ወዳጄ እንደ ምሳሌ እናንሣ ብንል እንኳ ተፈጥሮአውያን ስጦታዎች ከሆኑት መካከል አንዱና ዋነኛው ፆታዊ ፍቅር ነው።
  ወገኔ ሆይ ትዳር መልካም ነው፤ ነገር ግን ለትዳር ጓደኝነት ከውጫዊ ቁሳቁሶች በፊት ፍቅርን አስቀድም፡፡ ከዚያ በኋላ በትዳርህ ደስታና እረፍትን ታገኛለህ፡፡