ትርጉም በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
01/06/2004

ውስጣዊው የነፍሳችን ዐይኖች የበሩ
እንደሆነ ብቻ ነው የእግዚአብሔርን ሥራና ፈቃድ ማስተዋልና በሥነፍጥረትና በመጽሐፍ ቅዱስ ያሉትን ምሳሌዎችን መረዳት
የምንችለው፡፡ “ቅዱሳት መጻሕፍት ፊታችንን እንደምንመለከትባቸው
መስታወቶች ናቸው፡፡ ዐይኖቹ ብሩሃን የሆኑለት ሰው በእነርሱ ውስጥ እርሱ በእግዚአብሔር አርዓያና አምሳል እንደተፈጠረ ይረዳባችኋል፡፡” (ቅዱስ ኤፍሬም)
የማየት ብቃታችንም ሊያድግ የሚችለው እምነታችን ያደገና የጨመረ እንደሆነ ነው፡፡ የነፍስ
ዐይናችን በጣም ብርህት በሆነች ቁጥር እግዚአብሔራዊ እውነታዎችን በይበልጥ እየተረዳን እንመጣለን፡፡ አንዲት ነፍስ አንድን
እግዚአብሔራዊ እውነት በተለያየ አቅጣጫ መረዳት የቻለች እንደሆነ የዚህች ነፍስ ዐይኖች ብሩሃን ናቸው ማለት ነው፡፡