Monday, March 23, 2015

ቀጣይ መዝ.89 እንደ ቅዱስ ጀሮም

በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ 

14/07/2007

“የዘመኖቻችን እድሜ ሰባ ዓመት ነው…” አለን…. ግፋ ቢል ሰማንያ ብሎ ጨመረበት  ከሰማንያ ዓመት በላይ ብንኖር ግን ሕይወታችን ሕይወት ተብሎ የሚቆጠር አይሆንም፡፡ እንዲያም ቢሆን በጤና ሰማንያ ብንደርስ እድለኞች ነን፡፡ ከስምንት ዐሥር ዓመታት በኋላ ማን ነው ጤናማ ሆኖ የሚቀጥል?  ግሪካዊያን አንድ አባባል አላቸው፡- “እርጅና በራሱ አንድ የሕመም ዓይነት ነው” ይላሉ። ከሰማንያ ቢበዛ ግን ዳዊት “ድካምና መከራ ነው” እንዳለው ሃዘን ነው፡፡ 
እሰካሁን ድረስ ግን የመዝሙሩን ቀጥተኛ የሆነውን ትርጉም ነው የተመለከትነው፡፡ አሁን ደግሞ የቃሉን ምሥጢር እንመለከተው፡፡ ቢሆንም ሁሉን አንድ በአንድ አንመለከተውም እንዲያ ቢሆን ግን ጊዜ ባልበቃን ነበር፡፡ ስለዚህ ሌሎችን አልፈን ለምን የዘመናችን እድሜ ሰባ ዓመት ነው” አለ የሚለውን መንፈሳዊ ምስጢር ወይም መንፈሳዊ መልእክቱን ማየት እንጀምር፡፡ 
“የዘመናችን እድሜ ሰባ ዓመት ነው” አለ፡፡ ሰባ ቁጥር በሦስት እጥፍ አሥር ዓመታት ላይ አንድ ዐሥር ዓመት ያክላል፡፡ ዐራት እጥፍ ዐሥር ዓመታት ማለት ሰማንያ ዓመት ነው፡፡ ስለዚህ ቃሉ በሰባትና በስምንት ቁጥሮች ላይ ትኩረት መስጠቱን እንመለከታለን። እንዲሁ “አንተ ለትውልድ ሁሉ መጠጊያ ሆንህልን፡፡" ብሎ ትውልድ ያለው ብሉዩንና ሐዲስ ኪዳንን መሆኑን አስቀድመን እንዳስተማረንም ልብ በሉ፡፡ ልጁ ጠቢቡ ሰሎሞን  በመክበቡ “እንጀራህን በውኃ ፊት ጣለው ከብዙ ቀን በኋላ ታገኘዋለህ፡፡

መዝ.89 እንደ ቅዱስ ጀሮም ቀጣይ ክፍል


በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ

12/07/2007

አሁን ወደ መዝሙሩ ቃል እንመለስ፡- የእኛ የሕይወት ዘመን ለምሳሌ የሁላችን አባት የሆነው አዳም 930 ኖሮ ሞተ፡፡ ማቱሳላ ደግሞ 969 ዓመታት በሕይወት ቆይቶ ሞተ፡፡ እኚህ አባቶች አንድ ሺህ ዓመት ኖሩ ብንል እንኳ ለእኛ ከተሰጠን ዘለዓለማዊነት ጋር ሲነጻጸር እጅግ ኢምንት ነው፡፡ እንደ እውነቱ ከሆነ ፍጻሜ ያለው ነገር እንዴት ታላቅ ሊባል ይችላል? ኃጢአትን ሳንፈጽም እንድንኖር የተሰጠን 1000 ዓመት በአንተ ዘንድ እንደ አንዲት ቀን ነበረች፡፡  እንደ አንዲት ቀን ብቻ አለን? እንደ ሌሊት ትጋት ናት ብሎ ይበልጥ ኢምነት አደረጋት እንጂ፡፡ ስለሆነም ጌታችን ሆይ በአንተ ዘንድ ዘመኖቻችን የተናቁ ናቸው!! ስለዚህ ጌታ ሆይ ወደ አንተ እናጋጥጣለን፤ ሰውን ወደ ኅሳር አትመልሰው እንልሃለን፤ ጌታ ሆይ እኛን ለማዳን ወደ ምድር መምጣትህን፣  ደምህንም ስለእኛ መዳን ማፍሰስህን አስብ፡፡ ጌታ ሆይ አንተ ራስህ  “እኔ ከምድር ከፍ ከፍ ያልሁ እንደሆነ ሁሉን ወደ እኔ እስባለሁ”(ዮሐ.12፡32) ብለኸናልና  ጌታ ሆይ ! ራስህን ከፍ ከፍ አድርገህ እኛን ወዳንተ ሳብኸን እንጂ ወደ ላይ እንወጣጣ ዘንድ እኛ ወደ አንተ አልቀረብንምና አቤቱ ይህን አስብ፡፡