Tuesday, July 3, 2012

ስለድንግል ምልጃ ከመነገሩ በፊት የሚቀድመው ቁም ነገር!!!



በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
27/10/2004
ቅድስት ድንግል ማርያም ነጻ ፈቃዷን ተጠቅማ “ይኩነኒ በከመ ትቤለኒ” በማለት ለመዳናችን ምክንያት የሆነችን እናት ናት፡፡ እርሱዋ በአንደበቱዋ “ነፍሴ በእግዚአብሔር ደስ ይላታል መንፈሴም በአምላኬ በመድኀኒቴ ሃሴትን ታደርጋለች” ብላ እንደገለጠችልን ሥጋዋን ብቻ ሳይሆን  ነፍሱዋንና ሕሊናዋን ለጌታ ማደሪያ በማድረግ ለእኛ ክርስቲያኖች አብነት የሆነች የመጀመሪያይቱ ክርስቲያንና  አማናዊቱ ቤተክርስቲያን ናት፡፡
እኛም ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን በሥጋችን ቤተ መቅደስ፤ ሕጉንና ፈቃዱን እንዲሁም መንፈሱን በነፍሳችንና በሕሊናችን ማኅደር በማሳደር እርሱዋን እንመስላታለን፡፡ ስለዚህም ቅዱስ ጳውሎስ ስለእርሱዋና ስለእኛ በአንድነት ሲናገር“እንደ ንጽሕት ድንግል እናንተን ለክርስቶስ ላቀርብ ለአንድ ወንድ አጭቻችኋለሁ”አለን(2ቆሮ.12፡2)

ጸሎት ዘአረጋዊ ዮሐንስ



ትርጉም በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
27/10/2004 
ከእኔ የተሰወርክና የተሸሸግህ ጌታዬ ሆይ! አንተነትህን ግለጥልኝ ፡፡ ከእኔ ውስጥ ያለውን ያንተን ውበት አሳየኝ ፡፡ ሰውነቴ ለአንተ ማደሪያ ቤተ መቅደስ ይሆን ዘንድ የሠራኸው ጌታዬ ሆይ! (፩ቆሮ.፫፥፲፮-፲፯፤፪ቆሮ.፮፥፲፮)የክብርህ ደመና ቤተ መቅደስህ የሆነውን ሰውነቴን ይክደነው፤ የመሠዊያህም አገልጋይ የሆነችው ነፍሴ በፍቅር በመሆን አንተን ቅዱስ እያሉ በአድንቆትና በአግርሞት፣ በፍጹም ትጋትና ቅድስና እንደሚያገለግሉህ ሕያዋንና መንፈሳውያን ኃይላት ታመሰግንህ ዘንድ እርዳት፡፡…
የይቅርታ ውቅያኖስ የሆንክ ክርስቶስ ሆይ! ካንተ የሆነውን ብርሃናዊ ልብስ ተጎናጽፌ እንዳንጸባርቅ ባንተ ውኃነት በኃጢአት ያደፈውን ሰውነቴን እንዳጥብ ፍቀድልኝ፡፡ ሕቡዕ በሆኑ ምሥጢራት የተሞላው የክብርህ ደመና(መንፈስ ቅዱስ) እኔን ይከድነኝ ዘንድ (በእኔ ያድር ዘንድ) በዐይኔ ከማላያቸው ጀምሬ ወደ አንተ ውበት የሚወስዱኝን የጽድቅ ጎዳናዎች አስተውል ዘንድና ባንተ ግርማ ተማርኬ ያለማቋረጥ ክብርህን አደንቅ ዘንድ እንዲሁም በዓለም ጉዳይ ዐይኖቼ ከመባከን ያርፉ ዘንድ ምንም ቢሆን ምን ከአንተ ፍቅር የሚለየኝ እንዳይኖር ከዚህ ይልቅ አንተን በመናፈቅ እንድኖር ያለማቋረጥ ፊትህን እመለከት ዘንድ የልቡናዬን ዐይኖች ግለጥልኝ የልቡናዬንም እርሻ  አለስልሰው ፡፡”