Monday, August 31, 2015

የተመሰገነችው ድህነት በቅዱስ ኤፍሬም


ትርጉም ዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
25/12/2007

ቅዱስ ጳውሎስ "ኑሮዬ ይበቃኛል ለሚለው ግን እግዚአብሔርን መምሰል እጅግ ማትረፊያ ነው፤ ወደ ዓለም ምንም እንኳ አላመጣንምና፥አንዳችንም ልንወስድ አይቻለንም፤ ምግብና ልብስ ከኖረን ግን፥ እርሱ ይበቃናል።"(1ጢሞ.6:6-8) እንዳለው ክርስቶስን በመሰለና ለራስ በቂ በሆነ ሕይወት ውስጥ በመገኘት ናት በቅዱስ ኤፍሬም የተወደደችው ድህነት።
 ይህቺ ድህነት ሙሉ ትኩረትን እግዚአብሔርን ለመምሰል በሚረዱ ተግባራት መኖርን ትጠይቃለች።ይህ ነው ለቅዱስ ኤፍሬም ድህነት የሚለው ቃል ትርጉሙ።  ድህነት የሥጋ ድህነት ማለት አይደለም ለቅዱስ ኤፍሬም ይህ እንዳልሆነ እርሱ ራሱ በቃሉ  "ለሥራ ከመትጋት አትለግም ምንም እንኳ ባለጠጋ ብትሆን፥ ሰነፍ ሰው በሥራ ፈትነቱ  የተነሣ ቁጥሩ የበዛ ኃጢአትን ይፈጽማታልና" ብሎ ይመክራል። ስለዚህ ድህነት ማለት ለቅዱስ ኤፍሬም እንዲህ ከሆነ ድህነት ሳይሆን ድኅነት ነው።