Wednesday, December 13, 2017

የትርምት ሕይወት በቅዱስ ኤፍሬም(ክፍል ዘጠኝ) ቅዱሳት መጻሕፍትን ማንበብ

በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
04/04/2010
ወደ ቅድስና ሕይወት የሚመሩ ቅዱሳት መጻሕፍትን አድኖ ማንበብ አንዱ በትርምት ሕይወት ውስጥ የሚኖር ክርስቲያን ጠባይ ነው፡፡ የጥንት ክርስቲያኖች ክርስትናን በሕይወት ስለኖሩባት በጽሑፎቻቸው ሁሉ ክርስቲያናዊ ሕይወት ምን እንደሚመስል ከዲያብሎስ ጋር በምናደርገው ፍልሚያ ምን ማድረግ እንዳለብን በስፋት ጽፈውልን እናገኛለን፡፡
ቅዱስ ኤፍሬምም ከዲያብሎስ ወጥመድ ለማምለጥ ቅዱሳት መጻሕፍትን በጸሎትና ራስን ሰብስቦ በጥንቃቄ ማንበብ እንደሚገባ ያስተምራል፡፡ ቅዱስ አፍሬም እንደህ ማለቱ ዲያብሎስ አንባብያን የሚጠቅማቸውን ሰማያዊ ዕውቀት ከሚያነቡት መንፈሳዊ መጽሐፍ እንዳያገኙ ተግቶ ስለሚሠራና መልእክቱን አዛብተን በመረዳት ወደ ምንፍቅና እንዲንደረደሩ ስለሚያደርጋቸው ነው፡፡ ስለዚህ የንባብ ሕይወታችን እጅግ ጥንቃቄ የሚፈልግና በማስተዋል መፈጸም እንዳለበት ያሳስባል፡፡ እርሱም ሰይጣን እንዲህ አለ ብሎ በጻፈልን ጽሑፍ ላይ ይህንን እናስተውላለን፡፡
“እኔ ሰይጣን ስንፍናቸውን እንደሰንሰለት ተጠቅሜ ሰዎችን አ