Friday, December 20, 2019

ሞትን ማሰብ ደጉ


 በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ 

10/04/2012


ወገኖቼ ሞትን ማሰብ ደጉ እንዴት መረጋጋትን የሚሰጥ እሳቤን ይሰጠናል መሰላችሁ፡፡  ሞት ደጉን ስታስቡ በዚህ ዓለም የዘመን ቀመር ነገሮችን መቀመር ታቆሙና ነገሮችን በዘለዓለማዊው ዘመን ቀመር ይህም ትናንት ያይደለ ነገም ያልሆነ ለዘለዓለም አሁን ሆኖ በሚኖር ፀሐይ በማትወጣበትና በማትጠልቅበት በአምላክ ጊዜ ውስጥ ሆኖ አሁን አእምሮአችንን ሰቅዘው የያዙትን በሐሳብም፣ በቃልም፣ በተግባርም ያሉ ነገሮችን የምንመዝነበት ስለሆነ ሞት ደጉን አመስግኑት፡፡ እርሱን ማሰብ ባይኖር ኖሮ መች አምላክን መፍራት፣ ማፍቀር፣ መናፈቅ የዚህን ዓለም መከራ መዘንጋት መታገሥ እንዴት ገንዘብ እናደርጋቸው ነበር? ሞት ማሰብ ደጉ ሁሉን የሚያስተካክል፣ ትሑቱን ከፍ ከፍ የሚያደርግ፣ በትዕቢት የታጀረውን ማንም ሳያሰገድደው የሚያዋርድ፣ ባለሥልጣንንና ጦረኛን የሚያርድ ደፋሩን ፊሪ የሚያደርግ እንደ ሞትን ማሰብ ከቶ ምን አለ? ሞትን ማሰብ በስውር በሚያይ አምላክ ፊት በቅድስና ለመኖር አንቀጽ፣ የእውነተኛ ትሕትና እናት፣ የእውነተኛ ጸሎት መፍለቂያ ምንጭ ነው፡፡ ለዚህች መገኛ የገነት አምሳልነና በሯ ጾም ናት፡፡ አቤቱ አምላካችን ሆይ ሁሌም ቢሆን በፊትህ መሆናችንን እንድናስብ እርዳን፤ በሞት ወደ አንተ በጠራኸን ጊዜ እንዳናፍር በአንተ ዘንድ በጎ የሆኑትን ከማሰብ እስከ መፈጸም አብቃን፤ ወደ አንተም ስትጠራን “ኑዑ ኀቤየ ቡርካኑ ለአቡየ" ብለህ ተቀበለን፡፡    

Wednesday, December 11, 2019

ዳርዊን ቲዎሪውን ከየት አገኘው ?


በመ/ር ሽመልስ መርጊያ
ቀነን 01/04/2012


ወገኖቼ አንድ ነገር ልብ ብላችሁ አድምጡኝ፡፡ አንድ የካቶሊክ መነኩሴ ዳርዊን እርሱ የጻፈው ግልበጣ(ኩረጃ የራስ አስመስሎ ማቅረብ) መሆኑን ያስተዋለው ሰው ማን ነው? ከየት ብትሉኝ ከመጽሐፍ ቅዱስ ገልብጦ ብላችሁ ምን ትሉኛላችሁ? ግን እርሱ እግዚአብሔር በአርአያውና በአምሳሉ የፈጠረውን የሰው ልጅ ገልብጦ ዝንጀሮ አድርጎ ሴኩላር ቀለም ቀባው፡፡ እስቲ አስተውሉ፤ አዳምን የሠላሳ ዓመት ጎልማሳ ሔዋንን የዐሥራ አምስት ዓመት ኮረዳ አድርጎ የፈጠረ አምላክ ምድርና በውስጧ ያሉትን የቢልዮን ዓመታት ዕድሜ እንዲኖራቸው አድርጎ መፍጠር ይሳነዋል ብላችሁ ታስባላችሁን? እናም ወዳጆቼ ይህን ሐሳብ ከየት ስቦ እንዳመጣው ተገንዘቡ እርሱ መነኩሴ ነበር ማለት ስለመጽሐፍ ቅዱስ ጠንቅቆ ያውቃል ማለት ነው፡፡

Thursday, December 5, 2019

ተዋሕዶ ይቺ ናት


ተዛማጅ ምስልየጌታችን ጸያሔ ፍኖት (መንገድ ጠራጊ) ለቃል ድምፁ የሆነው ዮሐንስ መጥምቅ፡- “መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡበማለት የቅድስት ድንግል እናታችን ምሳሌ በሆነች በንስሐ ማኅፀን ተወልደንመንግሥተ ሰማያትወደ ተባለች የጌታ አካሉ እንገባ ዘንድ ሰበከን፡፡ ለጌታ ድምፁ የሆንኽ ቅዱስ ዮሐንስ ሆይ! ለአንተ በጊዜው ያልተፈጸመልህን ለእኛ የሰበክውን ይህን ድንቅ ዜና ይዘህ ስለመጣኽልን ፍጹም ደስ አለን፡፡ ይልቁኑ የኃጢአት ሥርየትን የመስጠት ስልጣን ያለው እርሱ ጌታችንመንግሥተ ሰማያት ወደሆነች ሰውነቴ በጥምቀቴ ባርኬ በሰጠኋችሁ ጥምቀት ከጎኔ በፈሰሰው ውኃ ነጽታችሁ ከጎኔም የፈሰሰውን ደሜን ተቀብላችሁ በጦር በተዋጋው ጎኔ ሽንቁር ዓለማችሁ ወደ ሆነው ወደዚህ መለኮታዊ አካሌ ግቡ እያለ ሰበከን፡፡ 

Monday, February 25, 2019

ጸሎት በኢትዮጵያውያን ሊቃውንት ትርጓሜ

በመ/ር ሽመልስ መርጊያ
18/06/2011 ዓ.ም  
ኢትዮጵያውያን ሊቃውንት እኔስ ቅዱሳን ብላቸው እመርጣለሁ በአንድነት የተስማሙባት አንዲት ደግ ትርጉም አለች እርሷንም በሕሊናዬ ሳደንቃት ሳወጣ ሳወርድ አረፈድኩ፡፡ እርሷም ጸሎት ማለት ከእግዚአብሔር ጋር መነጋገር ናት የምትለዋ ትርጓሜ ናት፡፡ እሊህ ሊቃውንት በአንድ ድምፅ ጸሎት ማለት ልመና፣ ምልጃ ወይም ምስጋና ማለት ነው ብለው አልተረጎሙልንም ነገር ግን ጻድቁ አብርሃም አምላኩን ሥላሴን በእንግድነት ተቀብሎ ያነጋገረውን ንግግር ዓይነት፣ ሎጥ ወንድሙንና ቤተሰቡን እንዲያድንለት ከአምላኩ ጋር የተነጋገረውን መነጋገር ዓይነት፣ ያዕቆብ በጵንኤል ከአምላኩ ጋር ታግሎ ካልባረከኝ አልለቅህም ያለውን ዓይነት መነጋገር፣ ሙሴ በደብረ ሲና ተራራ ላይ ዐራባ ቀንና ሌሊት ከፈጣሪው ጋር የተነጋገረበትን ዓይነት እና ክብርህን አሳየኝና እርሱ ይበቃኛል ብሎ የተነጋገረውን መነጋገር ዓይነት፣ ኤልያስ እና ኤልሳዕ ከአምላካቸው ጋር የተነጋገሩበትን መነጋገር ዓይነት፣ ነቢያት ሁሉ ከአምላክ ጋር የተነጋገሩትን መነጋገር ዓይነት ናት አሉን ወዳጆቼ፡፡

Friday, February 22, 2019

ተዋሕዶ ኅትመት


 መ/ር ሽመልስ መርጊያ 

ቀን 14/06/2011 ዓ.ም

አምላክ በሕይወት ካቆየኝ አንድ በጎ እና ለቤተ ክርስቲያን ቅናቱ ያለው ሰው ይህን ሐሳብ ከግብ ሊያደርሰው ይችላል ብዬ በማመን  ይህን ሕልሜን ለአንባቢያን ላከፍለው ወደድሁ 
 ስያሜ፡- ተዋሕዶ ኅትመት
የስያሜው ምክንያት፡- ተዋሕዶ ማለት በሁለት አካላት መካከል የተደረገ ፍጹም የሆነ አንድነትን የሚገልጽ ቃል ሲሆን አንዱ አካል እና የአካሉ ባሕርይ የሌላኛውን አካልና ባሕርይ ሳያጠፋ፣ ሳይመጥ፣ ሳይቀይር፣ ሳይቀይጥ፣ ሳይለውጥ ነገር ግን አንዱ አካል ሌላኛውን አካል የራሱ አካልና ባሕርይ በማድረግ አንድ አካል አንድ ባሕርይ በመሆን የሚገለጡበትን ምሥጢር ለማስረዳት ቤተ ክርስቲያናችን በብቸኝነት የምትጠቀምበት ቃል ነው፡፡ ይህ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከድንግል ማርያም ሰው ሆኖ በመወለድ የገለጠው ምሥጢር ነው፡፡ እርሱ እግዚአብሔር ቃል ከአብ ጋር በመተካከል ሲኖር ሳለ ሰውን ለማዳን ሲል ከቅድስት ድንግል ማርያም በጽንሰት ሥርዓት ከሥጋዋ ሥጋን ከነፍሷ ነፍስ በመንሳት ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው ሆኖ በአንድ አካልና በአንድ ባሕርይ ለፍጥረት ሁሉ ተገልጦአል፡፡ ይህን የእግዚአብሔር ቃል ሰው የመሆን ምሥጢር ቤተ ክርስቲያናችን ተዋሕዶ ትለዋለች፡፡ ይህንንም ቃል የራሷ መገለጫ ስም አድርጋም ትጠቀምበታለች፡፡ ይህንንም መጠሪያ ስሟ አድርጋ በመጠቀሟም ከሌሎች የክርስትና የእምነት ተቋማት ሁሉ ትለያለች፡፡  ስለዚህ ተዋሕዶ ስንል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ማለት እንደሆነ ማንም በቀላሉ ይገነዘበዋል፡፡ ለዚህም ነው ወደፊት እግዚአብሔር ቢፈቅድ እንዲመሠረት ለምፈልገው የሕትመት ተቋም ተዋሕዶ ኅትመት የሚል ስያሜ መስጠቴ፡፡   

Sunday, February 10, 2019

እግዚአብሔርን ማወቅ ራስን ለማወቅ


በመ/ር ሽመልስ መርጊያ

ቀን 03/06/2011 ዓ.ም

እውነቱን እንናገር ካልን ሰው ራሱን ወደ ማወቅ የሚደርሰው እግዚአብሔርን ወደ ማወቅ ሲደርስ ብቻ ነው፡፡ ሰው እግዚአብሔርን ሳያውቅ የሚኖረው ኑሮ ከእንስሳት በእጅጉ በተዋረደና ባለማስተዋል እንደ ሰይጣን ፈቃድና ሐሳብ በሆነ አኗኗር ውስጥ  ነው፡፡ ሰው ንጹሕ የሆነውን ባሕርይውን ተረድቶ ክፉ ፈቃዱን ገቶ በመልካም ሰብእና መመላለስ የሚችለው አስቀድሞ እግዚብአብሔርን ሲያውቅ ነው፡፡ አንድ ሰው ስለ እግዚአብሔር እየተማረ ሲያድግ ራሱን ወደ ማወቅ ይደርሳል፡፡ እግዚአብሔርን ሳያወቁ ራስን ማወቅ አይቻልም፡፡ ምክንያቱም ሰው በተፈጥሮው እግዚአብሔርን እንዲመስል ሆኖ የተፈጠረ ፍጥረት ነውና፡፡ ስለዚህ ሰው እግዚአብሔርን ሲያውቅ ንጹሕ የሆነውን እግዚአብሔርን የሚመስልበትን ባሕርይውን ወደ ማወቅ በእርሱም ወደ መመላለስ ይመጣል፡፡ እግዚአብሔርን በማወቅ ውስጥ ሆነን ራሳችንን ወደ ማወቅ ስንመጣ በውስጥም በውጪም ሥራ የሚሠራውን እግዚአብሔርንና ፈቃዱን እንረዳለን፡፡ እግዚአብሔርን ለማወቅ አለመሻት ራስን ለማወቅ ፈቃዱ እንደሌለን ማሳያ ነው፡፡  በራስ ጥረት ራስን ለማወቅ የሚደረግ ድካም  እንደው ደንዝዞ በስሜት መንሆለል፤ በሐሳብ መጋለብ፤ በምናብ መንጎድ ቢሆን እንጂ የትም አያደርሰንም፡፡ ይህም በድቅድቅ ጨለማ ውስጥ እንደመዳከር ነው፡፡

Tuesday, January 29, 2019

አማልክት ዘበጸጋ



ክብር ለእርሱ ለወደደን ይሁንና እርሱ እግዚአብሔር በእርሱ አርአያና አምሳል የፈጠረውን ሰውን ሊያልቀው በወደደ ጊዜ ከድንግል እናቱ ሞት የሚስማማውን የእኛን ባሕርይ ገንዘቡ አድርጎ ሰው ሆኖ ተወለደ፡፡ ከእርሷ የነሣውንም ሥጋና ነፍስ ባሕርይውን ሳይቀይር አምላክ አደረገው፡፡ በእርሱም በጌታችን በመድኀኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ሥጋዌ  በጸጋ እኛ የእግዚአብሔር አብ ልጆች፣ የእርሱ የጌታችን ወንድሞች የእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ሕፃናት ሆንን፡፡ በእርሱ በጌታችንም አማልክት ተሰኘን፡፡ ይህን ክብራችንን በትሩፋት ሥራዎች ከደከምን በዓይናችን ለማየት እንበቃለን፡፡ አረጋዊ መንፈሳዊ ከጌታ ጋር መዋሐዷ ስለተገለጠላት ትጉህ ነፍስ ሲጽፍልን፡-

Sunday, January 27, 2019

የካቲት ወር ምንባብ

የየካቲት ወር ጠዋት   የሚነበብ ንባብ 
የቀን.ቁ
1ኛ ምንባብ
2ኛ ምንባብ
ወንጌል
1
2ሳሙ.22
ፊልጵ.2
ዮሐ.1
2
2ሳሙ.24
ፊልጵ.4
ዮሐ.3
3
1ነገሥ.2
ቈላ.2
ዮሐ.5
4
ዘካ.7
የሐዋ.21፡1-14
ሉቃ.2፡22-40
5
1ነገሥ.5
1ተሰ.1
ዮሐ.8
6
1ነገሥ.7
1ተሰ.3
ዮሐ.10
7
1ነገሥ.9
1ተሰ.5
ዮሐ.12
8
ሚል.3፡1-5
ገላ.4፡1-11
ሉቃ.2፡22-40
9
1ነገሥ.12
2ተሰ.3
ዮሐ.15
10
1ነገሥ.14
1ጢሞ.2
ዮሐ.17
11
1ነገሥ.16
1ጢሞ.4
ዮሐ.19
12
1ነገሥ.18
1ጢሞ.6
ሉቃ.13፡1-9
13
1ነገሥ.20
2ጢሞ.2
ማቴ.2
14
1ነገሥ.22
2ጢሞ.4
ማቴ.4
15
2ነገሥ.2
ቲቶ.2
ማቴ.6
16
2ነገሥ.17
የሐዋ.13፡20-52
ሉቃ.1፡46-56
17
2ነገሥ.5
ዕብ.1
ማቴ.9
18
2ነገሥ.7
ዕብ.3
ማቴ.11
19
2ነገሥ.9
ዕብ.5
ማቴ.13
20
2ነገሥ.11
ዕብ.7
ማቴ.15
21
2ነገሥ.13
ዕብ.9፡1-10
ማቴ.17
22
2ነገሥ.15
ዕብ.10፡1-18
ማቴ.19
23
2ነገሥ.17
ዕብ.11፡1-16
ማቴ.21
24
2ነገሥ.19
ዕብ.12፡1-17
ማቴ.23
25
2ነገሥ.21
ዕብ.13
ማቴ.25
26
2ነገሥ.23
ያዕ.2
ማቴ.27
27
2ነገሥ.25
ያዕ.4
ማር.1
28
ዕዝ.2፡፡3፡፡
1ጴጥ.1፡1-12
ማር.3
29
ዕዝ.5
1ጴጥ.2
ማር.5
30
ዕዝ.7፡፡8፡፡
1ጴጥ.4፡1-11
ማር.7




የየካቲት ወር ማታ የሚነበብ ምንባብ
የቀን.ቁ
1ኛ ምንባብ
2ኛ ምንባብ
ወንጌል
1
2ሳሙ.23
ፊልጵ.3
ዮሐ.2
2
1ነገሥ.1
ቈላ.1
ዮሐ.4
3
1ነገሥ.3
ቈላ.3
ዮሐ.6
4
1ነገሥ.4
ቈላ.4
ዮሐ.7
5
1ነገሥ.6
1ተሰ.2
ዮሐ.9
6
1ነገሥ.8
1ተሰ.4
ዮሐ.11
7
1ነገሥ.10
2ተሰ.1
ዮሐ.13
8
1ነገሥ.11
2ተሰ.2
ዮሐ.14
9
1ነገሥ.13
1ጢሞ.1
ዮሐ.16
10
1ነገሥ.15
1ጢሞ.3
ዮሐ.18
11
1ነገሥ.17
1ጢሞ.5፡፡6፡፡
ዮሐ.20፡፡21፡፡
12
1ነገሥ.19
2ጢሞ.1
ማቴ.1፡፡
13
ነገሥ.21
2ጢሞ.3
ማቴ.3
14
2ነገሥ.1
ቲቶ.1
ማቴ.5
15
2ነገሥ.3
ቲቶ.3
ማቴ.7
16
2ነገሥ.4
ፊልሞ.1፡፡
ማቴ.8
17
2ነገሥ.6
ዕብ.2
ማቴ.10
18
2ነገሥ.8
ዕብ.4
ማቴ.12
19
2ነገሥ.10
ዕብ.6
ማቴ.14
20
2ነገሥ.12
ዕብ.8
ማቴ.16
21
2ነገሥ.14
ዕብ.9፡11-28
ማቴ.18
22
2ነገሥ.16
ዕብ.10፡19-39
ማቴ.20
23
2ነገሥ.18
ዕብ.11፡17-40
ማቴ.22
24
2ነገሥ.20
ዕብ.12፡18-29
ማቴ.24
25
2ነገሥ.22
ያዕ.1፡፡
ማቴ.26
26
2ነገሥ.24
ያዕ.3፡፡
ማቴ.28
27
ዕዝ.1
ያዕ.5፡፡
ማር.2
28
ዕዝ.4
1ጴጥ.1፡13-25
ማር.4
29
ዕዝ.6
1ጴጥ.3
ማር.6
30
ዕዝ.9፡፡10
1ጴጥ.4፡12-19
ማር.8