Tuesday, June 12, 2012

እምነት እውነት ፍቅር በክርስትና



በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
05/10/2004
አንድ በሀገራችን የነገሡ ንጉሥ ነበሩ፡፡ እኒህ ንጉሥ አንድ ወቅት “ልጅ ለአባቱ እምነት ለእናቱ እውነት ነው”ብለው ተናገሩ ይባላል፡፡ እንዲህ ብለው ከሆነ በእውነት ድንቅ የሆነን እውነት ተናገሩ፡፡ እኔ ግን እንዲህ እላለሁ፡፡ እግዚአብሔር አምላክ ሔዋን አዳምን ታውቀውና ታፈቅረው እንዲሁም እንደ እናትነቱና እንደ አባትነቱ ትታዘዘው ዘንድ፣ እርሱን ፈጥሮ ካበቃ በኋላ ልክ ልጅ ከእናቱ ተወልዶ በአካል እስኪገለጥ ድረስ ከእናቱ ሰውነት ውስጥ ተሰውሮ እንዲቆይ እንዲሁ በአዳም አካል ተሰውራ እንድትቆይ አደረጋት፡፡ እናት ልጁዋን በዐይን ለማየት እንድትናፍቅ እርሱዋን ለማየት አዳም በናፈቀ ጊዜ እግዚአብሔር ወልድ በሥጋ በመስቀል ላይ በተቀበለው ሕማም አርዓያ ሔዋንን ከአዳም ጎኑ አስገኛት፡፡ ስለዚህ ለአዳም አባታችን ሔዋን እውነቱ እንጂ እምነቱ አልነበረችም፡፡ እንዲሁም ሔዋን በአዳም አካል ውስጥ በነበረችበት ወቅት አዳም ፈጽሞ እንደሚወዳትና እንደሚያውቃት መጠን እርሱዋም እርሱን ፈጽማ ትወደውና ታውቀው ነበርና ለእርሱዋ አዳም እምነቷ ብቻ ሳይሆን እውነቷም ነው፡፡

Tuesday, June 5, 2012

"አባታችን ሆይ" በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የመጨረሻው ክፍል


ትርጉም በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ 
29/09/2004
...እርሱ ንጉሣችን ከሆነ ማን ያስፈራናል? ጌትነቱን ማንም ሊቃወምና ሊያጠፋ የሚቻለው የለም ፡፡ አርሱ  “መንግሥት የአንተ ናትና” ሲለን እኛን የሚዋጋውን ለጊዜ እግዚአብሔርን የሚቋቋም የሚመስለውን ሰይጣንን ለእኛ እንዲገዛ አሳልፎ እንደሚሰጠን ሲያመላክተን ነው ፡፡ እንደ እውነቱ ከሆነ እርሱ ከእግዚአብሔር ባሪያዎች አንዱ ነው ፤ ምንም እንኳ ከተዋረዱትና ለመተላለፋችን ምክንያት ከሆኑት ወገኖች ዋናው ቢሆንም ከላይ ከእግዚአብሔር ዘንድ ፈቃድ ካለገኘ በቀር በእግዚአብሔር ባሮች ላይ የማደር መብቱ የለውም፡፡ ስለምን  እኔ “ በባሮቹ ላይ” እላለሁ ፣ በእሪያዎች ላይ እንኳ በማደር እነርሱን አስቻኩሎና አጣድፎ ለማጥፋት ሰይጣን ከእግዚአብሔር ፈቃድን መቀበል የግድ አለበት (ማቴ.፯፥፲፬) በእንስሳት መንጋ ላይ እርሱ ካለፈቀደለት በቀር ከቶ ሊያድር ካልቻለ በሰው ልጆች ላይ እርሱ እግዚአብሔር ካልፈቀደ በቀር እንዴት ሊያድር ይችላል?


"አባታችን ሆይ"በቅዱስ ዮሐንስ አፈወረርቅ(ክፍል ዐራት)


“በደላችንን ይቅር በለን እኛ የበደሉንን ይቅር እንደምንል” 
ትርጉም በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
29/09/2004
ከአእምሮ በላይ የሆነው ምሕረቱን ትመለከታለህን ? እጅግ ታላላቅ የሆኑትን ክፋቶቻችንን ካስወገደልንና የእርሱን ታላቅ የሆነው ስጦታውን ከሰጠን በኋላ ሰው ዳግመኛ ቢበድል እንኳ በደላችንን  ይቅር ሊል ዝግጁ እንደሆነ በዘዚሀህ  ኃይለ ቃል አስታወቀን፡፡ ስለዚህም ይህ ጸሎት የአማኞች ጸሎት ይሆን ዘንድ በቤተክርስቲያን የጸሎት ሥርዐት ላይ መጀመሪያ የሚጸለይ ጸሎት ሆኖ ተሠራ፡፡
 ሰዎች ተጠምቀው ክርስቲያን ካልሆኑ በቀር እግዚአብሔር አብን አባት ብሎ መጥራት አይችሉም፡፡ ይህ ጸሎት እንግዲህ አማኞች ሊፈጽሙትና ሁሌም ሊጸልዩት  የሚገባ ጸሎት ከሆነ ቅዱስ ሥጋውና ቅዱስ ደሙን ከተቀበልን በኋላ ብንበድልና ንስሐ ብንገባ ንስሐችን ዋጋ እንደማያጣ ግልጽ ይሆንልናል፡፡ እንዲህ ባይሆን ኖሮ እንዲህ ብለን እንድንጸልይ  ሥርዐት ባልተሠራለን ነበር፡፡ ስለዚህም እርሱ ኃጢአታችንን እንድናስብና ይቅርታን እንድንጠይቅ እያሳሰበን እንዲሁም እንዴት ምሕረትን ማግኘት እንደምንችል እያስተማረንና ሸክማችንን በቀላሉ እንዴት ማቅለል እንደምንችል እያሳየን በምሕረቱ አጽናናን፡፡




Sunday, June 3, 2012

ጦማችንና ምጽዋታችን ምን ይምሰል? በቅዱስ ኤፍሬም



ርጉም በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
26/09/2004
መግቢያ
ለቅዱስ ኤፍሬምና ለሌሎችም የሶርያ ቅዱሳን አባቶች ጦም፣ ጸሎት እንዲሁም ምጽዋት ለነፍስ እንደ ብርሃን ናቸው፡፡ ዐይን ያለ ብርሃን ድጋፍ እንደማታይ እንዲሁ ነፍስም ያለእነዚህ ድጋፍ መንፈሳዊውን ዓለም መረዳት አትችልም፡፡ ጌታችንም “እንግዲህ ዐይንህ ጤናማ ብትሆን ሰውነትህ ብሩህ ይሆናል፡፡ ዐይንህ ግን ታማሚ ብትሆን ሰውነትህ ሁሉ የጨለመ ይሆናል፡፡ እንግዲህ በአንተ ያለው ብርሃን ጨለማ ከሆነ ጨለማውስ እንዴት ይበረታ!”(ማቴ.6፡22)በማለት ብርሃን ያላቸው እነዚህን ነው፡፡ እነዚህን በአግባቡና ከከንቱ ውዳሴ ተጠብቀን የፈጸመናቸው ከሆነ መንፈሳዊ ማስተዋላችን እጅግ የጠለቀ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ ነገር ግን እነዚህን ከሰው ክብርን በመሻት የፈጸምናቸው ከሆነ እነዚሁ ራሳቸው መልሰው ያጠፉናል፡፡
እነዚህ በአግባቡ ካልተገለገልንባቸው በኃጢአትችን ላይ ኃጢአትን እንድንጨምር ያደርጉናል፡፡ ስለዚህ በእኛ ያለው ብርሃን (ጦም፣ጸሎት፤ እንዲሁም ምጽዋት) በከንቱ ውዳሴና በሌሎችም ኃጢአት ጨለማ ከሆነ በፊት ከፈጸምናቸው ኃጢአት ጋር ተደምረው እኛን ወደ ጥልቁ ጨለማ ይጥሉናል፡፡ ስለዚህም ነው ጌታችን “ በአንተ ያለው ብርሃን ጨለማ ከሆነ ጨለማውስ እንዴት ይበረታ” ማለቱ፡፡ ይህን ድንቅ የሆነ አስተምህሮ እንድታስተውሉትና እኔ በትርጉሙ እንደተደነቅሁ በእናንተም ትደነቁ ዘንድ ቅዱስ ኤፍሬም ወንጌላትን ከተረጎመበት መጽሐፉ ያገኘሁትን ትርጓሜ እነሆ ብያችኋለሁ፡፡ በዚህ አጋጣሚ መጽሐፉን ገዝቶ በመላክ የተባበረኝን ወንደሜን ሙሉጌታ ሙላቱን ከልቤ ላመሰግነው እወዳለሁ፡፡   
ጌታችን ጦማችን ምን መምሰል እንዳለበት ሲያስተምር “እንደ ጦመኛ እንዳትታይ ራስህን ተቀባ ፊትህንም ታጠብ በስውር የሚያይ አባትህም በግልጥ ይከፍልሃል” አለን፡፡(ማቴ.6፡18)

Saturday, June 2, 2012

THE ASCETICAL TEACHING IN THE WRITINGS OF ST. EPHREM



By Shimelis Mergia
From senior essay
25/09/2004
The Ascetical teaching of St. Ephrem was just like St. Paul teaching to the Corinthian Christians, who taught about virginity.(1cor.7:11) such Ascetical life which introduced by St. Paul and later by St. Ephrem  is more biblical than Egyptian monasticism. St. Paul taught about virginity like this;
 “I say this concession, not as a command. I wish that all men were as I am but each man has his own gift from God; one has this gift anther has that. Now to the unmarried and the widows I say: it is good for them to stay unmarried” (1cor.7:6-8)
 According to St. Paul virginity is the preferable way of life to please God. But he couldn’t say marital life cannot be pleased God. However, it may have obstacles to serve God in whole life.

Friday, June 1, 2012

"አባታችን ሆይ"በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ (ክፍል ሦስት)


‹‹መንግሥትህ ትምጣ››
ትርጉም በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
25/09/2009
ይህም በጎ ሕሊና ያለው ሰው ጸሎት ነው፡፡ እንዲህ ዐይነት ሰው በዐይን በሚታዩ ምድራዊ ነገሮች የሚማረክ ሰው አይደለም፡፡ ወይም ይህን የሚታየውን ዓለም እንደ ትልቅ ቁምነገር የሚቆጥረው ሰው አይደለም፡፡ ነገር ግን ወደ አባታችን በጸሎት ይፋጠናል፡፡ከእግዚአብሔር ዘንድ የምትሰጠውንም መንግሥት ይናፍቃል፡፡ ይህ ፈቃድ ከመልካምና ከምድራዊ አመለካከት የተለየ ሕሊና ካለው ሰው ዘንድ የሚገኝ ነው፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ይህንን ሕይወት ዘወትር ይናፍቀው ነበር፡፡ ስለዚህም‹‹… የመንፈሱ በኩራት ያለን ራሳችን ደግሞ የሰውነታችን ቤዛ የሆነውን ልጅነት እየተጠባበቅን ራሳችን በውስጣችን እንቃትታለን››(ሮሜ.፰፡፳፫ )ብሏል፡፡ እንዲህ ዐይነት ናፍቆት ያለው ሰው በዚህ ምድር ባገኛቸው መልካም ነገሮች ራሱን አያስታብይም ወይንም በጽኑ መከራ ውስጥ ቢሆንም ከመከራው ጽናት የተነሣ አይመረርም ፡፡ ነገር ግን ወደ ሰማይ ወደ እረፍቱ ቦታ እንደገባ ሰው ምስቅልቅል ከሆነው ከዚህ ዓለም ሕይወት ነፃ የወጣ ሰውን ይመስላል፡፡