Friday, December 20, 2019

ሞትን ማሰብ ደጉ


 በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ 

10/04/2012


ወገኖቼ ሞትን ማሰብ ደጉ እንዴት መረጋጋትን የሚሰጥ እሳቤን ይሰጠናል መሰላችሁ፡፡  ሞት ደጉን ስታስቡ በዚህ ዓለም የዘመን ቀመር ነገሮችን መቀመር ታቆሙና ነገሮችን በዘለዓለማዊው ዘመን ቀመር ይህም ትናንት ያይደለ ነገም ያልሆነ ለዘለዓለም አሁን ሆኖ በሚኖር ፀሐይ በማትወጣበትና በማትጠልቅበት በአምላክ ጊዜ ውስጥ ሆኖ አሁን አእምሮአችንን ሰቅዘው የያዙትን በሐሳብም፣ በቃልም፣ በተግባርም ያሉ ነገሮችን የምንመዝነበት ስለሆነ ሞት ደጉን አመስግኑት፡፡ እርሱን ማሰብ ባይኖር ኖሮ መች አምላክን መፍራት፣ ማፍቀር፣ መናፈቅ የዚህን ዓለም መከራ መዘንጋት መታገሥ እንዴት ገንዘብ እናደርጋቸው ነበር? ሞት ማሰብ ደጉ ሁሉን የሚያስተካክል፣ ትሑቱን ከፍ ከፍ የሚያደርግ፣ በትዕቢት የታጀረውን ማንም ሳያሰገድደው የሚያዋርድ፣ ባለሥልጣንንና ጦረኛን የሚያርድ ደፋሩን ፊሪ የሚያደርግ እንደ ሞትን ማሰብ ከቶ ምን አለ? ሞትን ማሰብ በስውር በሚያይ አምላክ ፊት በቅድስና ለመኖር አንቀጽ፣ የእውነተኛ ትሕትና እናት፣ የእውነተኛ ጸሎት መፍለቂያ ምንጭ ነው፡፡ ለዚህች መገኛ የገነት አምሳልነና በሯ ጾም ናት፡፡ አቤቱ አምላካችን ሆይ ሁሌም ቢሆን በፊትህ መሆናችንን እንድናስብ እርዳን፤ በሞት ወደ አንተ በጠራኸን ጊዜ እንዳናፍር በአንተ ዘንድ በጎ የሆኑትን ከማሰብ እስከ መፈጸም አብቃን፤ ወደ አንተም ስትጠራን “ኑዑ ኀቤየ ቡርካኑ ለአቡየ" ብለህ ተቀበለን፡፡    

Wednesday, December 11, 2019

ዳርዊን ቲዎሪውን ከየት አገኘው ?


በመ/ር ሽመልስ መርጊያ
ቀነን 01/04/2012


ወገኖቼ አንድ ነገር ልብ ብላችሁ አድምጡኝ፡፡ አንድ የካቶሊክ መነኩሴ ዳርዊን እርሱ የጻፈው ግልበጣ(ኩረጃ የራስ አስመስሎ ማቅረብ) መሆኑን ያስተዋለው ሰው ማን ነው? ከየት ብትሉኝ ከመጽሐፍ ቅዱስ ገልብጦ ብላችሁ ምን ትሉኛላችሁ? ግን እርሱ እግዚአብሔር በአርአያውና በአምሳሉ የፈጠረውን የሰው ልጅ ገልብጦ ዝንጀሮ አድርጎ ሴኩላር ቀለም ቀባው፡፡ እስቲ አስተውሉ፤ አዳምን የሠላሳ ዓመት ጎልማሳ ሔዋንን የዐሥራ አምስት ዓመት ኮረዳ አድርጎ የፈጠረ አምላክ ምድርና በውስጧ ያሉትን የቢልዮን ዓመታት ዕድሜ እንዲኖራቸው አድርጎ መፍጠር ይሳነዋል ብላችሁ ታስባላችሁን? እናም ወዳጆቼ ይህን ሐሳብ ከየት ስቦ እንዳመጣው ተገንዘቡ እርሱ መነኩሴ ነበር ማለት ስለመጽሐፍ ቅዱስ ጠንቅቆ ያውቃል ማለት ነው፡፡

Thursday, December 5, 2019

ተዋሕዶ ይቺ ናት


ተዛማጅ ምስልየጌታችን ጸያሔ ፍኖት (መንገድ ጠራጊ) ለቃል ድምፁ የሆነው ዮሐንስ መጥምቅ፡- “መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡበማለት የቅድስት ድንግል እናታችን ምሳሌ በሆነች በንስሐ ማኅፀን ተወልደንመንግሥተ ሰማያትወደ ተባለች የጌታ አካሉ እንገባ ዘንድ ሰበከን፡፡ ለጌታ ድምፁ የሆንኽ ቅዱስ ዮሐንስ ሆይ! ለአንተ በጊዜው ያልተፈጸመልህን ለእኛ የሰበክውን ይህን ድንቅ ዜና ይዘህ ስለመጣኽልን ፍጹም ደስ አለን፡፡ ይልቁኑ የኃጢአት ሥርየትን የመስጠት ስልጣን ያለው እርሱ ጌታችንመንግሥተ ሰማያት ወደሆነች ሰውነቴ በጥምቀቴ ባርኬ በሰጠኋችሁ ጥምቀት ከጎኔ በፈሰሰው ውኃ ነጽታችሁ ከጎኔም የፈሰሰውን ደሜን ተቀብላችሁ በጦር በተዋጋው ጎኔ ሽንቁር ዓለማችሁ ወደ ሆነው ወደዚህ መለኮታዊ አካሌ ግቡ እያለ ሰበከን፡፡