Tuesday, April 17, 2012

“አብዝቶ የመመገብ ጣጣው” (በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)



ትርጉም ዲ/ንሽመልስ መርጊያ
09/08/2004
ከዚህ በፊት በማኅበረ ቅዱሳን ድኅረ ገጽ የተለቀቀ ጽሑፌ ቢሆንም ከጊዜው ጋር ተስማሚ ሆኖ ስላገኘሁት በድጋሚ አቅርቤዋለሁ

መግቢያ
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ የዮሐንስን ወንጌል በተረጎመበት በ፳፩ ኛው ድርሳኑ “ ጌታችን በእናታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ጥያቄ በቃና ሰርግ ላይ ስለምን ውሃውን ወደ ወይን ጠጅነት እንደቀየረው  ከአብራራ በኋላ ከዛሬ 1500 ዓመት በፊት በአሁኑ ጊዜ እንደ አዲስ ግኝት ተደርገው የሚታዩትን አብዝቶ በመመገብ የሚመጡትን የጤና ጉድለቶች ጽፎልን እናገኛለን ፡፡ ጽሑፉ ተተርጉሞ እንዲህ ቀርቦአል

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ውሃውን ወደ ወይን ጠጅነት ያኔ እንደቀየረ ዛሬም እኛን ድካማችንንና እንደ ወራጅ ውሃ በአንድ ቦታ ጸንቶ መቆየት የተሣነውን የሥጋ ፈቃዳችንን ከመቀየር አልተቆጠበም ፡፡ ዛሬም አዎን ዛሬም ልክ እንደውሃ ቀዝቃዛ ፣ደካማና ፣ ያልተረጋጋ ጠባይ ያለቸው ሰዎች አሉ ፡፡ እነዚህን ፈቃዶቻችንን ወደ ጌታችን አናምጣቸው ፤ እርሱ ወደ ወይንነት ይቀይራቸዋል  ፡፡  ከዚያም በኋላ ውኃ ሆነው ከእንግዲህ አይቀጥሉም ፡፡ ነገር ግን ለራሳቸውና ለሌሎች ደስታን የሚሰጡ አካላት ይሆናሉ ፡፡
በውሃ የተመሰሉት እነማን ናቸው ? ለዚህ ከንቱ ዓለም ሕሊናቸውን ያስገዙ ወገኖች ፣ የዚህን ዓለምን ቅምጥልነት ፣ አለቅነትንና ክብርን የሚሹ አይደሉምን ? እነዚህ ፍቃዶቻችን እንደውኃ የሚፈሱ ፣ ፈጽሞ ያልተረጋጉ ፣ ለአመፃ የሚፋጠኑ ቁልቁል የሚምዘገዘጉ ውኆች ናቸው ፡፡

የትንሣኤው መልእክት



በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
09/08/2004
ቅዱስ ጳውሎስ “ፋሲካችሁ ክርስቶስ ታርዶአልና ስለዚህ በቅንነትና በእውነት በዓልን እናድርግ እንጂ በአሮጌ እርሾ በክፋትና በግፍ እርሾ አይደለም”(1ቆሮ.5፡8)አለን፡፡ በዚህ ቦታ በክርስቶስ የተሰበከችውን ወንጌል በእርሾ መስሎ ማስተማሩን እናስተውላለን፡፡ ስለዚህም ለእኛ ክርስቲያኖች የሕይወት ዘመናችን በሙሉ የበዓል ቀን ነው፡፡(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ) ቅዱስ ጳውሎስ “በዓል እናድርግ” ሲለን ግን እንደ አይሁድ የዳስ በዓልን ወይም ከግብጽ ባርነት ነጻ የወጡበትን ፋሲካቸውን ማለቱ እንዳልሆነ ሁላችንም መረዳቱ አለን፤ አስቀድሜ እንደ ተናገረኩት እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ለሚነሡ ሁሉ የሚበቃ የእግዚአብሔር በግ ክርስቶስ ታርዶአልና በዓልን አድርጉ ሲለን ነው፡፡
 ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለእኛ ካለው ጥልቅ ፍቅር የተነሣ ራሱን አንድ ጊዜ መሥዋዕት አድርጎ በማቅረቡ ከጨለማ ወደሚደንቅ ብርሃን፣ ከባርነት ወደ ነጻነት፣ ከድሮው አዳማዊው ተፈጥሮ ክርስቶስን ለብሰን ወደምንገኝበት ሰብዕና አሸጋግሮናል፡፡ እነሆ በእርሱ የድኅነት ሥራ ሀገራችን በሰማይ ሆኗል፡፡ ስለዚህም አነጋገራችን፣ አመጋገባችን፤ አለባበሳችን፤አኗኗራችን ሁሉ ተለውጦአል፡፡ ከእንግዲህ ደስታችን በምድራዊው ምግብና መጠጥ አይደለም፡፡ ነገር ግን ልክ እንደ ቅዱሳን መላእክት መንፈስ ቅዱስ በሚሰጠን መጽናናት ሆኖአል፡፡ ጌታችን ለእኛ ካደረገው ከዚህ ታላቅ ቸርነት በላይ ሌላ ቸርነት አለን? ስለእኛ መዳን ሲል እግዚአብሔር ቃል ሰው ሆነ፤ስለእኛ ጭንቅ የሆነ ሕማምን ተቀበለ፣ በሞቱ ሞትን አጥፍቶ እኛን ከሰይጣን ባርነት ነጻ አውጥቶ አዲስ ሕይወትን ሰጠን፡፡ ሰውነታችን ማደሪያው ቤተመንግሥቱ ሆነ፡፡