Tuesday, July 31, 2012

St. Epherm said about us



By Shimelis mergia.
25/11/2004

“The King’s Son,(Jesus Christ) when he saw her wickedness came and betrothed to Himself the church(that means we are) … whose love and truthiness He had tested, He made her one with Himself, that there might be not separation. See, she sits in the King’s palace, dressed in the ornaments of the King. The month Nisan serves her,(the crucifixion of Him on the Cross) arrayed and adorned with flowers. Glory to You, Lord of Nisan (Passover "
ፋሲካ”)"
But now we men, when we saw the women who adorned with the glory of King and sat on the palace of glory, we desire them to be our wives, who by whom sanctified and cleansed and washed with Water and Word, and made them without spot and wrinkle. We felt by the beauty of their holiness and Glory. So we asked our beloved God like our former father Adam, to give them to us as wives like this:- “This is now bone of my bones, and flesh of my flesh; she shall be called Woman, because she was taken out of Man (the Second Adam Christ)” Oh what amazing mystery is it Oh men !!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!! Gory to you oh God, Glory to the women who adorning themselves with true Christianity!!!
የንጉሥ ልጅ የሆነው እርሱ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የእርሷን መተላለፍ ተመልክቶ ቤተ ክርስቲያንን የራሱ ትሆን ዘንድ አጫት፡፡(ቤተ ክርስቲያንም የተሰኘነው እኛ ነን) የእርሷን ለእርሱ ያላትን ፍቅርና ታማኝነት ፈትኖ ከእርሱ አካል ጋር አዋሐዳት፡፡ ይህች ቤተ ክርስቲያን በንጉሥ ጌጣጌጦች ተውባ ከንጉሥ ቤተ መንግሥት መቀመጫዋን እንዳደረገች አስተውል፤ የኒሣ ወርም ታገለግላታለች፡፡( በመስቀሉ የሰጣት ምሥጢራት እርስዋን ያገለግሏታል)(ቅዱስ ኤፍሬም)
(እኔ ደግሞ ይህን አልኩበት ታቸችያለወውን ጨርከኩበት) 

እኛ ወንዶችም በንጉሥ ክርስቶስ አጊጠውና  ከንጉሥ ቤተ መንግሥት ከብረው የተገኙትን በመስቀሉ በፈጸመው ቤዛነት በቃሉና በተቀደሰው ውኃ ንጹሕ ያደረጋቸውን ሴቶች ስንመለከት የእኛ ሚስቶች የሆኑ ዘንድ ተመኘን፡፡  በእነርሱ ቅድስናና ግርማ ተማርከን ወደቅን፡፡ ስለዚህ ሰውን ወዳጅ የሆነውን እግዚአብሔርን እንደ ቀድሞው አዳም “እነዚህ ሴቶች ከሥጋችን ሥጋ ከአጥንታችን አጥንት ናቸውና በዚህም ምክንያት ሴቶች ተብለዋል፡፡ ምክንያቱም እነዚህ ሴቶች ከዳግማዊው አዳም ክርስቶስ የተገኙ ናቸውና፡፡ እናንት ወንዶች ሆይ ይህ ምሥጢር ምን የሚደንቅ! አምላካችን ሆይ ለዚህ ድንቅ ሥራህ ምስጋና  ይገባሃል፤ በእውነተኛ ክርስትና ራሳቸውን ያስጌጡ ሴቶችም ምስጋና ይገባቸዋል ለዘለዓለም በእውነት፡፡
 
 

Saturday, July 28, 2012

“ሽሽታችሁ በክረምት ወይም በሰንበት አይሁን”(በቅዱስ ኤፍሬም)የመጨረሻ ክፍል



ትርጉም በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
22/11/2004 ዓ.ም
ጌታችን “በሰገነት ላይ ያለ ወደ ኋላ አይመለስ”(ሉቃ.17፡31) በሚለው ኃይለ ቃሉ በእነርሱ ላይ ቁጣው ምንም የነደደ ቢሆንም የእነርሱን ጥፋት እንደማይወድ ያሳየበት ኃይለ ቃል ነው፡፡ “በዚያችም ወራት ለርጉዞች ለሚያጠቡ ወዮላቸው”(ማቴ.24፡19) ሲልም በጊዜው ስለፀነሱት ሴቶች ልጆቻቸው እየተናገረ ሳይሆን በሮማዊያን ጭንቅ የሆነ መከራን ትቀበላላችሁ ሲላቸው ነበር፡፡ ስለዚህም “ችግር በምድር ላይ በዚህም ሕዝብ ላይ ይሆናል”(ሉቃ.21፡23)ብሎ ተናገረ፡፡ በዚህም ምክንያት “ሽሽታችሁ በክረምት ወይም በሰንበት እንዳይሆን ጸልዩ” በማለት ከዚህ መከራ እንዲድኑ ጌታችን አስጠነቀቃቸው፡፡ እንዲህም ሲል የጽድቅን ሥራ የማትሠሩባት ቀን ትመጣለች፡፡ በዚያች ዕለት መብራታችሁን ከዘይታችሁ ጋር ሳትይዙ እንዳትገኙ፤ ይህም ማለት ፍቅርን ከምጽዋትና ከንጽሕና ጋር ወይም እምነትን ከምግባር ጋር ሳትይዙ እንዳትገኙ ተጠንቀቁ በዚያች በመጨረሻዋ ሰዓት ለመብራታችን ዘይት እንፈልግ በማለት ያም ማለት የትሩፋት ሥራዎችን እንሥራ ብትሉ አይቻላችሁም፤ ምክንያቱም ጊዜው የሥራ ሳይሆን የፍርድ ጊዜ ነውና፡፡(ማቴ.25፡1-13) ስለዚህም ጽድቅን ሳትሠሩ ጊዜው ፈጥኖ እንዳይደርስባችሁና እንዳይፈረድባችሁ በጸሎት ትጉ ሲል “ሽሽታችሁ በክረምት ወይም በሰንበት እንዳይሆን ተጠንቀቁ” አላቸው፡፡ በክረምት ፍሬ እንደሌለ በሰንበትም ሥራ የለም፡፡ ስለዚህም ሽሽታችሁ በክረምት ወይም በሰንበት አይሁን ሲል እምነትንና ምግባርን ሳትይዙ ድንገት ምጽአቱ እንዳይደርስባችሁ በጸሎት ትጉ ሲል ነው፡፡

“ሽሽታችሁ በክረምት ወይም በሰንበት አይሁን”(ትርጉም በቅዱስ ኤፍሬም)



ትርጉም በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
21/11/2004 ዓ.ም
ተወዳጆች ሆይ ዛሬ ጌታችን “እንግዲህ በነቢዩ በዳንኤል የተባለውን የጥፋት ርኩሰት በተቀደሰችው ሥፍራ ቆሞ ስታዩ አንባቢው ያስተውል”(ማቴ.24፡15) የሚለውን ኃይለ ቃል ትርጉም እንማማራለን፡፡ እንደሚታወቀው ኢየሩሳሌም ብዙ ጊዜ ጠፍታ በተደጋጋሚ መልሳ የተገነባች ከተማ ናት፡፡  ነገር ግን ይህ የትንቢት ቃል በኢየሩሳሌም የአምልኮው ሥርዐቱና በሌዋውያን ካህናት የሚቀርበው መሥዋዕት ፈጽሞ እንደሚቋረጥ የሚያስረዳ ኃይለ ቃል ነው፡፡ አስቀድሞ በነቢዩ ዳንኤል “የጥፋት ርኩሰት” የተባለውን አንዳንድ ተርጓሚያን  “ሮማውያን በቤተመቅደሱ እሪያ በመሠዋት ጭንቅላቱን ይዘው ወደ ቅድስተ ቅዱሳኑ እንደሚገቡና መቅደሱን እንደሚያረክሱት፤ ይህ በተፈጸመ ጊዜ የኢየሩሳሌም ጥፋት እንደቀረበ አንባቢው ያስተውል ሲል ነው ብለው ይተረጉሙታል፡፡(ፍጻሜው ግን ቅዱስ ጳውሎስ “እኔ እግዚአብሔር ነኝ ብሎ አዋጅ እየነገረ በእግዚአብሔር ቤተመቅደስ እስኪቀመጥ ድረስ አምላክ ከተባለው ሁሉ ሰዎችም ከሚያመልኩት ሁሉ በላይ ራሱን ከፍ ከፍ የሚያደርገው ተቃዋሚ እርሱ ነው” ብሎ የተናገረለት የሐሳዊው መሲህ መገለጥ ነው፡፡(2ተሰ.1፡4)

Thursday, July 26, 2012

Christian philosophy on women and men interaction.



By Shimelis Mergia
19/11/2004
The spiritual understanding has a power to adjust the ideologies of secular thoughts. Those how are guading in natural law live like animals. Spiritual understanding for them foolihness. But we Christian can see above this. Our undertanding is above natural laws. We understand any thing in the help of Holy Spirit who is the creator of all created beings. so our thinking can shape the secular thoughts which are focused on the natural law only.
 Women have more tendencies to spiritual things than men. Beside others, they want to learn spiritual things from men. Unless otherwise, if men are not learn them piritual things beside others, they may hate them suggesting as one of the fornicetors who desiring their flesh. 
Their eyes looking from down to top but we men are looking from to down.
 Or they pull us down to earthily things; we also pull up them to heavenly things. This is natural law. Then both of us become in medium. That is the correct place of human beings. Human being is mediator, to visible and invisible creation.
Do you see the gravity which planted by God in our nature? Anybody cannot be escaped from the gravity of earth, until he stops to live on earth. Such like things; we couldn’t escape from the gravity of that God planted inside our nature until we live on earth. We men and women are pulling each other to live in the medium life.

ቅዱስ ገብርኤል ሆይ እስቲ ልጠይቅህ!


በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
19/11/2004
ዛሬ የጌታችንንና የአፍቃሪያችንን የኢየሱስ ክርስቶስን መልክና ግርማ ለብሶ በብሉይ ኪዳን ለቅዱሳን መጽናናትን ይሰጥ የነበረውና(ዳን.10፡5-5 ከ ራእይ.1፡14-16 ካለው ጋር ያነጻጽሩ፤ እንዲሁም ሕዝ. 1፡26 ከ ዳን.8፡15፤9፡21፤10፡18 እንዲሁም 3፡25 ያነጻጽሩ)በሐዲስ ኪዳንም የድኅነት ብሥራትን ይዞ ወንድሞቻችንን መላእክትን ወክሎ እንዲሁም ነፍስን በደስታ በምታስጨንቅ ፍስሐ ተሞልቶ፣(ሉቃ፡15፡10) ወደ ድንግል በመምጣት ሕዝቡን ከኃጢአት የሚያድናቸው የስሙ ትርጓሜ መድኀኒት የሆነውን "ኢየሱስን በድንግልና ጸንሰሽ በድንግልና ትወልጃለሽ"(ሉቃ፡1፡31) ብሎ ያበሠረ የተወዳጁ መልአክ የቅዱስ ገብርኤል ክብረ በዓል ነው፡፡
 ሰውና አምላክ ፍጹም እርቅን የፈጸሙባትን ያቺን ዕለት ሳስባት ነፍሴ በሐሴት ትሰክራለች፡፡ ልጅ ከእናትና ከአባት ጥምረት ይወለዳል ፡፡ ስለዚህ ልጅ የእናትና የአባት ውሕደት አማናዊ መገለጫ ነው፡፡ እንዲሁ እግዚአብሔር አብ ለእኛ ያለውን ጥልቅ ፍቅር ሊገልጥልን ስለወደደ ልጁን እግዚአብሔር ወልድን ከድንግል በሥጋ ይወለድ ዘንድ ላከው፡፡  ልጁም ከእናታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሱዋ ነፍስ ነስቶ በመወለድ ፍጹም እርቅ በሰውና በእግዚአብሔር  መካከል መፈጸሙን በልደቱ አበሠረን፡፡ 
ከአባት አብራክና ከእናት መኀፀን የተወለደን ልጅ አካፍሎ ወደፊት ለአባትና ለእናት መስጠት እንዳይሞከር እንዲሁ እግዚአብሔር ወልድ ከእናታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም በሥጋ ከተወለደ በኋላ አምላክ ወሰብእ ተብሎ ይኖራል እንጂ ወደፊት ተከፍሎ የለበትም፡፡

Sunday, July 22, 2012

ሰው ማለት ምን ማለት ነው?


በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
15/11/2004
(ከዚህ በፊት በማኅበረ ቅዱሳን መካነ ድር የተለቀቀ)
ሰው ማለት ነፋሳዊነት፣ እሳታዊነት፣ ውኃዊነት፣ መሬታዊነት ባሕርያት ያሉት በነፍስ ተፈጥሮውም ነባቢት ለባዊትና ሕያዊት የሆነች ነፍስ ያለችው ፍጥረት ነው፡፡ እንዲህ ብለን ግን የሰውን ተፈጥሮ ጠቅልለን መናገር አይቻለንም፡፡ ምክንያቱም ሰውን ከሌሎች ፍጥረታት ይልቅ እጅግ ልዩ በሆነ መልኩ በእግዚአብሔር አርአያና አምሳል ተፈጥሮአልና፡፡ ስለዚህም ቅዱሳን አባቶች ከዚህ በላይ ከሰጠነው ትንታኔ በመውጣት እንዲህ ብለው ሰው ለሚለው ስያሜ ትርጓሜ ይሰጡታል፡፡

Saturday, July 21, 2012

ለፍቅር መምህር የሆነ ፍቅር እና ወዳጄ ሆይ .....


በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
14/11/2004
ጾታዊ ፍቅር በራሱዋ ንጽሕትና ቡርክት እንዲሁም ቅድስት ናት፡፡ በዚህ ፍቅር የወደድካትን ካገኘሃት፤ ይህች ፍቅር በልብህ ውስጥ ርኅራኄን፣ አክብሮትን፣ትዕግሥትን፣ አርቆ አሳቢነትን ስትዘራብህ ታገኛታለህ፡፡ ከአጣሃት ግን ከልብህ ስለማትወጣ እስከ ነፍስህ ህቅታ ድረስ በልብህ ሃዘንን ተክላ ትኖራለች እንጂ ፈጽማ አትጠፋም፡፡ወላጆች ሆይ ልጆቻችሁ ባለገንዘብ እንዲሆኑ ከመድከም ይልቅ ወደ እግዚአብሔር ባሕርይ የምታቀርባቸውን ይህችን ፍቅር በሕይወታቸው አግኝተዋት አእምሮአቸው ብሩህ ሆኖ ፍቅር የሆነውን አምላካቸውን እንዲያውቁትና እንዲያፈቅሩት ለዚህ ሕይወታቸው ትጉላቸው!!! እናንተ በእውነተኛይቱ ፍቅር ተጣብቃችሁ አንድ አካል ወደ መሆን የመጣችሁ ጥንዶች ሆይ! ንጽሕት፣ ቡርክት፣ ቅድስትና የእግዚአብሔር ፍቅር ፍጣሬ ብርሃን በሆነችው በዚህች ፍቅር ታግዛችሁራስን ለሚወዱት አሳልፎ እስከመስጠት ወደሚያደርሰውየክርስቶስ ፍቅር ታድጉ ዘንድ ምኞቴ ነው፡፡ ለዚህች ፍቅር እንደ መጥምቁ ዮሐንስ አዋጅ ነጋሪዎች ትሆኑም ዘንድ ምኞቴ ነው፡፡ አቤቱ አንተነትህን በዚህች በማንነታችን ውስጥ በጥልቀት በተከልካት ፍቅር እንድናውቅና በእንባ ሆነን በፍቅር እንድናመልክህ ይህችን ፍቅር በተፈጥሮአችን የሠራሃት አንተ ለዘለዓለም የተመሰገንክ ሁን፡፡ በዚህች ፍቅር ጠብን እንድናጠፋትና ፍቅርህን ለብሰን እንድንገኝ ጌታ ሆይ እርዳን ለዘለዓለሙ አሜን፡፡




Monday, July 9, 2012

መካከለኛ(አማላጅ) ለሚለው ጥያቄ የተሰጠ ምላሽ፡፡


በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
1/11/2004
እንደ ወረደ አቅርቤዋለሁ ያንብቡትና የራሶን አስተያየት ያኑሩበት

"What is the role of your priest (pastor)? What is the job of him? Why do you want him led you to Christ your Lord? is that the bible said "እንግዲህ እግዚአብሔር በእኛ እንደሚማልድ ስለክርስቶስ መልእክተኞች ነን ከእግዚአብሔር ጋር ታረቁ ብለን ስለክርስቶስ እንለምናለን"? (2ቆሮ.5:20) Christ our Lord is the Good shepherd. But He gave the power of shepherd to Apostles.(Mtt.18:18, John.21:15-19 and 20:19 ) apostles also gave the power of shepherd to their followers.(Act.20:28) they sat the rule how ordain the bishops, priest and deacons.(1Tim.3:1-13) if they didn't play the mediator role, what is the necessity of these all ordinations? Is it not biblical?

ስለስብከት ወተግሣጽ መጽሐፌ በመጠኑ


ከዚህ መጽሐፍ የተቀነጨቡ

መግቢያ

ኤፍሬም አጭር የሕይወት ታሪክ

ቅዱስ ኤፍሬም በሦስተኛው ክፍለ ዘመን በመጀመሪያዎቹ ሰባት አሥርተ ዓመታት ውስጥ የኖረ የሥነ መለኮት ሊቅ ፣ የዜማ ደራሲ ፣ ባለቅኔ ፣ ሰባኪ ፣ የቅዱሳት መጻሕፍት ተርጓሚ የሆነ ጻድቅ አባት ሲሆን ፣ በጊዜው በሮም መንግሥት ሥር በነበረችው በሶርያ ንጽቢን 1 በምትባለው ታላቅ ከተማ ከክርስቲያን ቤተሰብ  በ፪፻፺፱ ዓ. ም ተወለደ ፡፡
በዘመኑ ሊቀ ጳጳስ በሆነው በቅዱስ ያዕቆብ ዘንጽቢን 2፣ ባደገባት ከተማ ፣ የዲቁና ማዕረግ ተሹሞ በከተማዋ በምትገኝ ቤተክርስቲያን አገልጋይ ዲያቆን ሆነ ፡፡



Saturday, July 7, 2012

የቤተ ክርስቲያንን ለቤተ ክርስቲያን የገዳምን ለገዳማውያን



በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
29/10/2004
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቅዱስ ጴጥሮስ …ትወደኛለህን? ብሎ ከጠየቀውና እርሱም አዎን ብሎ ከመለሰ በኋላ “... ግልገሎቼን አሰማራ…ጠቦቶቼን ጠብቅ … በጎቼን አሰማራ” ብሎ መንጋውን እንዲጠብቅ አደራ እንደሰጠው እናውቃልን፡፡(ዮሐ.19፡15-17)ይህ ሓላፊነት ምንም እንኳ ለእርሱ ይነገረው እንጂ ለሐዋርያት ሁሉ የተሰጠ ሓላፊነት ነበር፡፡ እነርሱም የክርስቶስን መንጋ ከሥጋና ከመንፈስ ርሃብ ጠብቀው የድርሻቸውን ተወጥተው አልፈዋል፡፡ ቤተ ክርስቲያን ማለት ሕጻናት፣ ወጣቶችና አረጋዊያን በአንድነት የሚኖሩባት፣ በምድር ያለች ግን ሰማያዊት፤ ቅዱሳን መላእክት፣ ቅዱሳን ነፍሳትና በምድር ያለነው በጥምቀት ከክርስቶስ ጋር በሞቱ ለዚህ ዓለም ኃጢአት የሞትን፤ መንፈስ ቅዱስ በሚሰጠን ሕይወት ሕያዋን የሆንንና በትንሣኤ ሕይወት የምንመላለስ የምንኖርባት፤ ጌታችን መድኀኒታችን የሚገዛትና የሚመራት ከምድር እስከ ሰማይ የተተከለች ዘለዓለማዊት መንግሥት ናት፡፡ ገዳም ግን መነኩሳት በፈቃድ የብሕትውናን ሕይወት መርጠው የሚኖሩባትና ለእነርሱ ብቻ የምትስማማ ሆና ሥርዐት የተበጀላት መንፈሳዊት ሥፍራ ናት፡፡


Wednesday, July 4, 2012

ዳግማዊቱ አዳም


በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
28/10/2004
ክርስቲያኖች ሆይ ከቅዱስ ኤፍሬም ጋር መንፈሳዊ ቅኔን እንቀኝ፡፡ እርሱ ስለቅድስት ድንግል ማርያም እንዲህ ይላልአዳም ለሔዋን እናትም አባትም እንደነበር እንዲሁ ቅድስት ድንግል ማርያም ለልጁዋ ለወዳጁዋ እናትም አባቱም ሆነች፡፡” ከዚህ ተነስተን  አዳም የሚለው መጠሪያ ለድንግልም የሚያገለግል እንደሆነ እንረዳለን፡፡ ስለዚህ አዳም ስንል ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ማለታችን እንደሆነ ሁሉ እንዲሁ አዳም ስንል ቅድስት ድንግል ማርያም ማለታችንም ነው፡፡በእርግጥ ጥንትም አዳም የሚለው መጠሪያ ስም ለወንዱ ብቻ የሚያገለግል መጠሪያ ሰም አልነበረም “እግዚአብሔር አዳምን በፈጠረበት ቀን ወንድና ሴት አድረጎ ፈጠራቸው ባረካቸውም፡፡ ስማቸውንም በፈጠረበት ቀን አዳም ብሎ ጠራቸው” ይላልና፡፡(ዘፍ.5፡2) እነሆ አዳም የሚለው መጠሪያ ስም ለሴቶችም እንደሆነ እንረዳ ዘንድ ቅድስት ድንግል ማርያም እንደ አዳም ለጌታችን ለመድኀኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ እናትም አባትም ሆና አሳደገችው፡፡ ይህ ምሥጢር ሌላም እውነታን በውስጡ አዝሎ ይዟል፡፡ እርሱም፡- በክርስቶስ አምነን የእርሱ የአካሉ ሕዋሳት ለሆነውና በእርሱ አካል ለምንገለጠው ክርስቲያኖችም( ሮሜ.12፡5) ቅድስት ድንግል ማርያም እናትም አባትም መሆኑዋን እንረዳለን፡፡ ኦ ጌታችን ሆይ!!! ይህ እንዴት ድንቅ የሆነ ምሥጢር ነው!!!

Tuesday, July 3, 2012

ስለድንግል ምልጃ ከመነገሩ በፊት የሚቀድመው ቁም ነገር!!!



በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
27/10/2004
ቅድስት ድንግል ማርያም ነጻ ፈቃዷን ተጠቅማ “ይኩነኒ በከመ ትቤለኒ” በማለት ለመዳናችን ምክንያት የሆነችን እናት ናት፡፡ እርሱዋ በአንደበቱዋ “ነፍሴ በእግዚአብሔር ደስ ይላታል መንፈሴም በአምላኬ በመድኀኒቴ ሃሴትን ታደርጋለች” ብላ እንደገለጠችልን ሥጋዋን ብቻ ሳይሆን  ነፍሱዋንና ሕሊናዋን ለጌታ ማደሪያ በማድረግ ለእኛ ክርስቲያኖች አብነት የሆነች የመጀመሪያይቱ ክርስቲያንና  አማናዊቱ ቤተክርስቲያን ናት፡፡
እኛም ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን በሥጋችን ቤተ መቅደስ፤ ሕጉንና ፈቃዱን እንዲሁም መንፈሱን በነፍሳችንና በሕሊናችን ማኅደር በማሳደር እርሱዋን እንመስላታለን፡፡ ስለዚህም ቅዱስ ጳውሎስ ስለእርሱዋና ስለእኛ በአንድነት ሲናገር“እንደ ንጽሕት ድንግል እናንተን ለክርስቶስ ላቀርብ ለአንድ ወንድ አጭቻችኋለሁ”አለን(2ቆሮ.12፡2)

ጸሎት ዘአረጋዊ ዮሐንስ



ትርጉም በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
27/10/2004 
ከእኔ የተሰወርክና የተሸሸግህ ጌታዬ ሆይ! አንተነትህን ግለጥልኝ ፡፡ ከእኔ ውስጥ ያለውን ያንተን ውበት አሳየኝ ፡፡ ሰውነቴ ለአንተ ማደሪያ ቤተ መቅደስ ይሆን ዘንድ የሠራኸው ጌታዬ ሆይ! (፩ቆሮ.፫፥፲፮-፲፯፤፪ቆሮ.፮፥፲፮)የክብርህ ደመና ቤተ መቅደስህ የሆነውን ሰውነቴን ይክደነው፤ የመሠዊያህም አገልጋይ የሆነችው ነፍሴ በፍቅር በመሆን አንተን ቅዱስ እያሉ በአድንቆትና በአግርሞት፣ በፍጹም ትጋትና ቅድስና እንደሚያገለግሉህ ሕያዋንና መንፈሳውያን ኃይላት ታመሰግንህ ዘንድ እርዳት፡፡…
የይቅርታ ውቅያኖስ የሆንክ ክርስቶስ ሆይ! ካንተ የሆነውን ብርሃናዊ ልብስ ተጎናጽፌ እንዳንጸባርቅ ባንተ ውኃነት በኃጢአት ያደፈውን ሰውነቴን እንዳጥብ ፍቀድልኝ፡፡ ሕቡዕ በሆኑ ምሥጢራት የተሞላው የክብርህ ደመና(መንፈስ ቅዱስ) እኔን ይከድነኝ ዘንድ (በእኔ ያድር ዘንድ) በዐይኔ ከማላያቸው ጀምሬ ወደ አንተ ውበት የሚወስዱኝን የጽድቅ ጎዳናዎች አስተውል ዘንድና ባንተ ግርማ ተማርኬ ያለማቋረጥ ክብርህን አደንቅ ዘንድ እንዲሁም በዓለም ጉዳይ ዐይኖቼ ከመባከን ያርፉ ዘንድ ምንም ቢሆን ምን ከአንተ ፍቅር የሚለየኝ እንዳይኖር ከዚህ ይልቅ አንተን በመናፈቅ እንድኖር ያለማቋረጥ ፊትህን እመለከት ዘንድ የልቡናዬን ዐይኖች ግለጥልኝ የልቡናዬንም እርሻ  አለስልሰው ፡፡”