Thursday, January 24, 2019

የመጥምቁ ዮሐንስ ቃል(ክፍል አንድ)



በመ/ር ሽመልስ  መርጊያ 

ቀን 17/05/2011 ዓ.ም

ጌታዬ ሆይ በኣቴ በሆነች በእናቴ ማኅፀን ሳለሁ ሥራዬ አንተንና አንተን ማሰብ ብቻ ነበርና ወደ እኔ የምትመጣበትን ቀን በጉጉት እጠባበቅ ነበር፡፡ ምክንያቱም ገና ስጸነስ ጀምሮ የአንተ ባሪያና መንገድ ጠራጊ እንድሆን አድርገህ ስለፈጠርኸኝ አንድ ቀን ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ እንዳለህ አውቅ ነበርና፡፡ እናም ገና የስድስት ወር ጽንስ ሳለሁ አንተ የእለት ጽንስ ሆነህ በእንግድነት ከእናትህ ጋር ወደ እኔ ስትመጣ ስጠብቀው የነበረ ተፈጽሞአልና ሊነገር በማይችል ደስታ ውስጥ ሆኜ ተቀበልኩህ፡፡ ጌታ ሆይ በቅድስት እናትህ የሰላምታ ድምጽ እንዳንተ በማሕፀን ላለሁት ለእኔ ሰላምህን ሰጥተኸኛልና አንተን በማወቄ ዕውቀቴ ገና ከማሕፀን ሳልወጣ ፍጹም ሆነ፡፡ ምክንያቱም አንተ የዕውቀት ፍጻሜ ነህና፡፡ ስለዚህ ከአንተ ከአባትህ ከእግዚአብሔር አብ ከባሕርይ ሕይወትህ ከመንፈስ ቅዱስ ሌላ ሌላ መምህር አላስፈለገኝም፡፡