Monday, January 14, 2013

ክርስትና ለእኔ እና እኔ አልስማማም እንዲሁም….



በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
07/05/2005
ለእኔ ክርስትና ማለት ምን ማለት ነው ቢሉኝራስ መሆንብዬ እመልሳለሁ፡፡ በምን ሲባል ከኃጢአት በቀር በሁሉ ብዬ እመልሳለሁ፡፡ ከዚያ በኋላ ዕረፍት አለን፡፡ ክርስትና ድህነት ማለት አይደለም፡፡ ነገር ግን ስለፍቅርና ስለቅንነት እኛ ያለንን እንደ ችሎታችን የጠየቁንን ስለምንሰጥ ለሥጋዊው ድህነት የቀረብን ነን፡፡ ቢሆንም በሥራ ያን ጉድለት እንደፍነውና ለምጽዋት እጃችንን እንዘጋለን፡፡ ነገር ግን ለሁሉ ማለትም ለምድራዊውም ለሰማያዊውም ሀብታችን ምንጩዋ ቤተክርስቲያን ብትሆን መልካም ነበር፡፡ በእርሱዋ በኢኮኖሚም ሆነ በሥነ ልቡና የደከሙት ተጠነካክረው ለዓለም እንደ ብርሃን በመሆን በእነርሱ መልካም ሥራ የእግዚአብሔር ስም ሊመሰገን ይገባው ነበር፡፡