Monday, March 26, 2018

ቅዱሳን ሆይ ለምኑልን



  በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
መጋቢት 17 ቀን 2010 ዓ.ም
ሰውነታችሁን በእውነት በጽድቅ ሕይወት ቤተ መቅደስ አድርጋችሁ እርሱ የሁሉ ጌታ የሆነ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅድስተ ቅዱሳን በሆነች ነፍሳችሁ መንገሡ የሚታወቃችሁና እርሱን አውቃችሁ እጅግ ትሑታን ሆናችሁ የምትመላለሱ ቅዱሳን ሆይ እናንተ ንዑዳን ክቡራን ናችሁ፡፡ የእናንተ ጭንቀት በሰውነታችሁ መቅደስ በቅድስተ ቅዱሳን ውስጥ ነግሦ ያለውን ጌታ አለማሳዘን የሆነ በሕሊናችሁ ውስጥ ስለምታሰላስሉት ሓሳብ እንኳ የምትጠነቀቁ ቅዱሳን ሆይ እናንተ ንዑዳን ክቡራን ናችሁ፡፡ እናንተ በሦስት አጥሮች ራሳችሁን አጥራችሁ ግርማውን እያያችሁ እንደ ቅዱሳን መላእክት በፍርሃትና በርዓድ ሆናችሁ በእርሱ ፊት ዘወትር የምትቆሙ ቅዱሳን ሆይ በእውነት እናንተ ንዑዳን ክቡራን ናችሁ፡፡ 

Wednesday, January 17, 2018

በዓለ ጥምቀት


በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
ጥር ፲ ቀን ፳፻፲

 

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
ለመላው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን በሙሉ እንኳን ለጌታችን ለመድኀኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል በሰላም አደረሰችሁ!!

የጌታችን አካሉ የሆነች የፍቅር እናት ቤተ ክርስቲያን በዛሬው እለት የእግዚአብሔር አብ ልጅ ለሆነው ለእግዚአብሔር ወልድ የታጨችበት የሙሽርነቷን ጊዜ በታላቅ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዓት በድምቀት ታከብራለች፡፡ ይህች ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ማሕፀንና ማየ ገቦው ባደረጋት የጥምቀት ውኃ በጌታዋ ያመኑትንና የመንጎቿን ልጆችን በ፵ እና በ፹ ቀናቸው በማጥመቅ የጌታዋ የአካሉ ሕዋስ በማድረግ ከሕያዋን ቅዱሳን መላእክት፣ ከቅዱሳን ነፍሳት፣ ከበኩራት ማኅበር ጋር ማኅበርተኛ ታደርጋቸዋለች፡፡ ይህንን ከጌታዋ በሐዋርያቶቿ በኩል ተቀበለች ፡፡ በእነርሱ ስልጣንም ሰማያውያን ደናግላንን እለት እለት በኅቱም ድንግልና ትወልዳለች፡፡ ከንጉሡም ማዕድ ስሙ በሰፈረበት በምሕረት ኪዳኑ ወይም መሠዊያው ታቦቱ ላይ የተፈተተውን ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን ትመግባቸዋለች፡፡