Saturday, May 20, 2017

ምጽዋትና ጥቅሟ በሊቃውንት አባቶቻችን

በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
12/09/2009Oዓ.ም

እባካችሁ ከዚህ ጽሑፍ የታዘባችሁትን ጻፉልንኝ

(ከፍትሐ ነገሥት ላይ የተወሰደ)

ምጽዋትስ ከርኅራኄ ወገን ነው፡፡ ይኸውም ሰው በገንዘቡ ምጽዋትን ለሚሹት ሰዎች የሚያደርገው ርኅራኄ ነው፡፡ ከእነርሱ ዘንድ ትርፍ ሳይሻ ጌታችን “ገንዘባችሁን ሽጣችሁ ለድሆች ምጽዋት ስጡ” ብሎ ስላዘዘ ነው “የማይጠፋ ኮረጆ አድርጉ የማይጠፋ የማያልፍ ሰማያዊ ድልብ አከማቹ”(ሉቃ.12፡23) እንዲሁም ዳግመኛም ጌታችን ምጽዋትን ስጡ ሁሉም ንጹሕ ይሆንላችኋል አለ፡፡
ሰው በምጽዋት በሚቻለው መጠን ፈጣሪውን ይመስለዋል፡፡ ምጽዋትና መራራት ከአምላክ የተገኘ ባሕርይ ነውና፡፡ ጌታችንም “እንደ ሰማያዊ አባታችሁ የምትራሩ ሁኑ አለ”(ማቴ.5፡48) ምጽዋትሰ አምላካዊት ብድር ናት፡፡ ይህችውም የታመነችና የምትረባ አምላካዊት ንግድ ናት፡፡ ይህችውም ዳግመኛ ወዶ እስኪወስዳት ድረስ ብልህ ሰው ከፈጣሪው ከእግዚአብሔር ዘንድ የሚያኖራት አደራ ናት፡፡ ይህችውም ዳግመኛ በነባቢት መቅደስ ዘንድ ተቀባይነት ያላት ቁርባን ናት፡፡ እግዚአብሔርም ስም አጠራሩ ከፍ ከፍ ይበልና መሥዋዕትን ያይደለ ምጽዋትን እሻለሁ” አለ”(ሆሴዕ.6፡6፤ማቴ.9፡13) ዳግመኛም ከእርሱዋ ጋር ጾም ተቀባይነት ያለው ይሆናል፡፡ ነቢዩ እንደተናገረ(ኢሳ.58፡6-7)ጸሎትን ከርሷ ጋር ይቀበላል፤ በቆርነሌዎስ እንደተነገረ፡፡ ያለርሷ ድንግልናም አትጠቅምም በአምስቱ ሰነፎች ደናግል እንደ ተጻፈ”(ማቴ.25፡11-12)