Sunday, March 26, 2017

ምጽአቱ ለክርስቶስ


በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
17/07/2009


ወዮ ይህች ከእውነተኛ ጌታ የወጣች ትምህርት እንዴት ታስፈራለች ? እርሱ  ስለትንሣኤ ሕይወታችን በዐሥሩ ደናግላን መስሎ አስተማረን እንዲህም አለን፥-"በዚያን ጊዜ" ያላት ያችን የምታስፈራዋን የምጽአቱን ቀን ነው።  በዚያን ጊዜ መንግሥተ ሰማያት መብራታቸውን ይዘው ሙሽራውን ሊቀበሉ የወጡ አሥር ቆነጃጅትን ትመስላለች" አለን። በአሥሩ ደናግላን የተመሰልነው እኛ በጥምቀት ለክርስቶስ የታጭነው ክርስቲያኖችን ነን። ስለሆነም ጌታችን ክርስቲያን መሆናችን ብቻ እንደማያድነን እምነትን ከምግባር፥ እምነትን ከፍቅር ጋር፥ እምነትን ከጦም ከጸሎት ከስግደት ከምጽዋት ጋር አብረን አስተባብረን ይዘን የብርሃን መላእክትን መስለን ራሳችንን ከኃጢአት ጠብቀን የጌታን መምጣት በናፍቆት እንጠብቅ ዘንድ እንዲገባን ሊያስተምረን እንዲህ አለን።

Tuesday, March 21, 2017

ሦስት አጫጭር ጹሑፎች

በዙሪያችን ያሉ መምህራን

አንድ ኦርቶዶክስ ክርስቲያን ልማር ካለ በዙሪያው የሚያስተምሩት አሉለት። ከዋኖቹና ከማይሳሳቱ ሊሳሳቱ እስከሚችሉት መምህራን በቅደም ተከተል ልንገራችሁ ፥-
የመጀመሪያው መንፈስ ቅዱስ ነው። እርሱ ልጅነትን ከተቀበልንበት ጊዜ አንስቶ መምህራችን ነው። ሁለተኛው ሥጋው ወደሙ ነው። ሥጋው ወደሙን የሚቀብል ሰው ሁሌም ወደላይ ወደ መላእክት ጉባኤ በመነጠቅ ክርስቶስን ወደ ማወቅ ከፍታ እያደገ እንደ ቅዱስ ጳውሎስ ለሰዎች ሊነገር የማይገባውን ሰምቶ ይመለሳል። ያም ማለት ክርስቶስ ባለበት እርሱ በዚያ ይኖራል። ሌላው ከጠባቂ መላእክት ነው። እነርሱ ከእኛ አይለዩም ስለእኛ በእግዚአብሔር ፊት ይቆማሉ እንድን ዘንድ ያለንን ማስተዋልንንና እውቀትን በመስጠት ይረዱናል። ያዕቆብን በመከራው ጊዜ የተራዳው እርሱ ጠባቂ መልአኩ ነበር። አብርሃምን ያስተማረው ለዳንኤል እውቀትንና ማስተዋልን የሰጠው እርሱ ነው ሌላው  በመንፈስ ቅዱስ መሪነት የተጻፉ መጻሕፍት ናቸው እነዚህ ለአንድ ኦርትዶክስ ክርስቲያን  ከተጠቀመባቸው መምህራኖቹ ናቸው። ከዚያ በኋላ ልንሳሳት የምንችለው እኛ መምህራን እንከተላለን። 
ቢሆንም ግን ክብር ይግባውና የእግዚአብሔርን ድምጽ  እናውቀዋለንና አዲስም ቢሆን ከእግዚአብሔር የሆነውና ያልሆነውን የምንለይበት ሕሊናና መንፈስ ቅዱስ አለን። በዚህ ሁሉ ውስጥ ሆኖ ከእውቀት ባዶ ሆኖ መገኘት ይከብዳል።

Saturday, March 4, 2017

"ወደ ዕረፍቱ የገባ ከሥራ አርፎአል"



በዲ/ሽመልስ መርጊያ
25/06/2009

ቅዱስ ጳውሎስ፥- "የነቢያትም መናፍስት ለነቢያት ይገዛሉ"(1ቆሮ.14:32)ሲል መቼም ስለመንፈስ ቅዱስ እንዳልሆነ ግልጽ ነው። ለአጋንንትም አይደለም። እርግጥ ነው ሐዋርያት በአጋንንት ላይ ስልጣን አላቸው። ቢሆንም ግን ይህ ቃል ስለ አጋንንት የሚናገር አይደለም ስለቅዱሳኑ መላእክት እንጂ።  እና ቅዱሳን መላእክት ለነቢያት ይገዛሉ እንዴ?  የሚል ጥያቄን ሊያስነሣም ይችላል። ፡በፍጹም እንዲያ ቢሆን ነቢያት የእግዚአብሔር መልአክ ሲገለጥላቸው እግዚአብሔር እንደተገለጠላቸው ቆጥረው ባልሰገዱላቸውና ባልታዘዙላቸው ነበር። እንደ አብነት ለኢያሱ የእግዚአብሔር መልአክ ተገልጦለት ነበር። እንዲያም ቢሆን ቅዱሱ መልአክ ለኢያሱ አልተገዛም። እንዲሁ ለነቢዩ ዳንኤል ቅዱስ ገብርኤል በሰው አምሳል ተገልጦለታል። ሲገለጥለት ግን እውቀትንና ማስተዋልን ይሰጠው ዘንድ ነበር። ዳንኤልም ለመልአኩ መስገዱ ተጽፎልናል። ጌታችንም በእርሱ ፊት ስለሚቆሙት ሰለጠባቂ መላእክት ስንል ታናናሾችን እንዳንንቅ አስጠንቅቆናል። ለካህኑ ዘካርያስ፥ ለዮሴፍ፥ ለእናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ቅዱስ ገብርኤል ተገልጦአል። አንድም ቦታ ግን ስለመገዛቱ አልተጻፈም።