Thursday, December 7, 2017

የትርምት ሕይወት በቅዱስ ኤፍሬም (ክፍል ስምንት)


በመ/ር ሽመልስ መርጊያ
29/03/2010

ለቅዱስ ኤፍሬም ድህነት ማለት ሁሉ የሚገኝባት ሰማያዊ ግምዣ ቤት ናት፡

“በዚህች የከበሩ ነገሮች ሁሉ በሚቀመጡባት ግምዣ ቤተ ተደነቅሁ፤ በውስጧ ያሉ የከበሩ ሀብታት ሁሉ ከሁሉ ይልቅ ክቡራን ናቸው፡፡  ከሀብቶቿ ሊያጎልባት የሚችል አንድም ሰው የለም፡፡ ለዚህች ግምዣ ቤት የብዕሏ ምንጭ ድህነት ናት ፡፡ ነገር ግን ሰዎች በዙሪያዋ ከትመውባታል ከዚህች ግምጃ ቤት ሃብትም ይናጠቃሉ፡፡ ንጥቂያ እንደመሆኑ መጠን ብዙዎች ባለጠጎች ሆኑባት፡፡ በዚች ሕይወት ለጸኑትና አጥብቀው ላሿት ሀብቷ በኃይልና በብዛት ይፈሳል” በማለት ድህነትን የሰማያዊ ሀብት ግምዣ ቤት እንደሆነች ሲሰብክ እናገኘዋለን፡፡ ስለዚህ እንደ ቅዱስ ኤፍሬም ከዚህ ሀብት ይናጠቁ ዘንድ ክርስቲያኖች ክርስቶስን በሁሉ ሊመስሉ ይገባቸዋል፡፡ እርሱ ነውና የጸጋ ሁሉ ግምጃ ቤት ባለቤቱ፡፡ እርሱን ስንመስል ከእርሱ ዘንድ ባለ ሰማያዊ ሀብት ባለጠጎች እንሆናለን፡፡ የዚህንም አላፊ ጠፊ የሆነውን ዓለም ሀብት እንድንንቀው ያደርገናል፡፡ በዚህ ሕይወት ከተገኘንም መንፈስ ቅዱስ ሕይወታችንን ይመራዋል፡፡ እንዴት መኖር እንዳለብንም እወቀቱ ከእርሱ እናገኛለን፡፡