Wednesday, May 30, 2012

‹‹አባታችን ሆይ››በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ(ክፍል አንድ)


                          
v ግብዞችን አትምሰሉአቸው
ትርጉም በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
23/09/2004
ግን ስትጸልይ ወደ እልፍኝህ ግባና መዝጊያህንም ዘግተህ በስውር ላለው አባትህ ጸልይ በስውር የሚያይህ አባትህ በግልጽ  ይከፍልሃል፡፡››(ማቴ.፮᎓፩−፮)
በዚህ ቦታ ላይ ጌታችን  ኢየሱስ ክርስቶስ ጻፎችንና ፈሪሳዊያንን ግብዞዎች ማለቱ አግባብነት ነበረው፡፡ ምክንያቱም ወደ እግዚአብሔር ቤት ለጸሎት በሚመጡበት ጊዜ የሰዎችን ቀልብ ለመሳብ ሲሉ ከሥርዐት የወጣ አለባበስን ይለብሱ ነበር እንጂ ለጸሎት ተስማሚ የሆነውን የትሕትና አለባበስን አይለብሱም ነበርና ነው፡
ለጸሎት ወደ አምላኩ የሚቀርብ ሰው ሌሎች ጉዳዮቹን ሁሉ ወደ ኋላ ትቶና ከሰው ዘንድም ምስጋናንና ክብርን ሳይሻ ጸሎቱን ተቀብሎ ወደሚፈጽምለት አምላኩ ብቻ ትኩረቱን ሊያደርግ ይገባዋል፡፡ይህን መፈጸም ትተህ አይኖችህን  የትም የምታንከራትት ከሆነ ከእግዚአብሔር ቤት በባዶ እጅህ ምንም ሳታገኝ እንድትመለስ እወቅ፡፡ከእግዚአብሔር አምላክ ዘንድ ዋጋ ማግኘትና ማጣት በእጅህ የተሰጠ የአንተ እድል ፈንታህ ነው፡፡ ስለዚህ ከንቱ ውዳሴን የሚሹ ሰዎች ከእኔ ዘንድ አንዳች አያገኙም አላለም ፡፡ነገር ግን‹‹ ዋጋቸውን ተቀብላዋል››አለ፡፡