Friday, December 28, 2012

እኔ ከመጽሐፍ ቅዱስ ይልቅ ራሱ መንፈሱ የእምነት ምንጭ ነው እላለሁ



ከዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
19/04/2005
በመጽሐፍ ብቻ የሚለው አመለካከት ለእኔ  ትክክል አይመስለኝም፡፡ ከመጽሐፍ ይልቅ በልብ ሰሌዳ በመንፈሱ የተጻፈ የመንፈስ ቅዱስ መልእክት አለ፡፡ መንፈሱ ያደረበት ሰው የማይመረመረውንና የማያልቀውን የእግዚአብሔርን ሃሳብና ፈቃድ ወደ መረዳት ይመጣል ሁሌም መንፈስ ቅዱስ ሰማያዊ የሆኑ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ ያልሰፈሩ ወይም ያልተብራሩ እውነታዎች ይገልጥለታል፡፡
 በብሉይም በሐዲስም የእግዚአብሔር ፈቃድና ሃሳብ በወረቀት ላይ በብዕር ቀለም መጻፍ ያስፈለገበት ምክንያት ሰዎች አስቀድሞ እግዚአብሔር በመንፈሱ በልባቸው ጽላት ላይ የጻፈውን ፈቃዱንና ሕጉን በኃጢአት ምክንያት ፈጽመው በመዘንጋታቸው ነው፡፡ ስለዚህም መጽሐፍ ቅዱስ ሰዎች ፈቃዱን አውቀው በጽድቅ ይመላለሱ ዘንድ የተሰጠ ሁለተኛው እድል ነው፡፡ ለዚህ ማሳያው ከአዳም እስከ ሙሴ ድረስ ያሉ ቅዱሳንና ሐዋርያት እንዲሁም ሐዲስ ኪዳን ሳይጻፍላቸው በሐዋርያት ትምህርት ይኖሩ የነበሩ ቅዱሳን ክርስቲያኖች ናቸው፡፡