Sunday, January 22, 2017

"ሥጋን ለበሰ" ማለት ትርጉሙና ምንጩ?


ዲ/ን ሽመልስ መርጊያ 
14/05/2009
በአበው ሊቃውንት ዘንድ የቃል ሥጋ መሆን ወይም የሥጋ አምላክ መሆን ለማስረዳት ሲሉ “ሥጋ ለበሰ” የሚለውን ቃል መጠቀም የተለመደ ነው፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስ “ለበሰ” የሚለው ቃል እንደ አገባቡ የራሱ የሆነ ትርጉም አለው፡፡ ልብስ ለበሰ፣ ኤፉዱን ለበሰ፤ ኃይልን ለበሰ ወዘተ የሚሉ ዐረፍተ ነገሮችን በተለይ በኦሪቱ በስፋት ተጽፎ እናገኘዋለን፡፡ ነገር ግን ይህን በምንረዳበት መንገድ ከታች ያሉትን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች መረዳት አንችልም፡፡ ለምሳሌ፡- “እግዚአብሔርም ምድርን እነሆ ተበላሸች ሥጋን የለበሰ ሁሉ በምድር ላይ መንገዱን አበላሸቶ ነበርና”(ዘፍ.6፡12) የሚል ቃል አለ፡፡ በዚህ ሥፍራ “ሥጋን የለበሰ ሁሉ” ሲል ሥጋን እንደ ልብስ የለበሰ ማለት ሳይሆን “ሰው የሆነ ሁሉ” ማለቱ እንደሆነ ለሁሉ ግልጽ ነው፡፡