Thursday, December 5, 2019

ተዋሕዶ ይቺ ናት


ተዛማጅ ምስልየጌታችን ጸያሔ ፍኖት (መንገድ ጠራጊ) ለቃል ድምፁ የሆነው ዮሐንስ መጥምቅ፡- “መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡበማለት የቅድስት ድንግል እናታችን ምሳሌ በሆነች በንስሐ ማኅፀን ተወልደንመንግሥተ ሰማያትወደ ተባለች የጌታ አካሉ እንገባ ዘንድ ሰበከን፡፡ ለጌታ ድምፁ የሆንኽ ቅዱስ ዮሐንስ ሆይ! ለአንተ በጊዜው ያልተፈጸመልህን ለእኛ የሰበክውን ይህን ድንቅ ዜና ይዘህ ስለመጣኽልን ፍጹም ደስ አለን፡፡ ይልቁኑ የኃጢአት ሥርየትን የመስጠት ስልጣን ያለው እርሱ ጌታችንመንግሥተ ሰማያት ወደሆነች ሰውነቴ በጥምቀቴ ባርኬ በሰጠኋችሁ ጥምቀት ከጎኔ በፈሰሰው ውኃ ነጽታችሁ ከጎኔም የፈሰሰውን ደሜን ተቀብላችሁ በጦር በተዋጋው ጎኔ ሽንቁር ዓለማችሁ ወደ ሆነው ወደዚህ መለኮታዊ አካሌ ግቡ እያለ ሰበከን፡፡