Monday, July 6, 2015

የዘፍ.1፡1-4 ልዩ ምልከታ



በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ 
29/10/2007

ተወዳጆች ሆይ ሌላም ግሩም የሆነውን በቅዱሳን አባቶች ዘንድ ያለውን ትርጓሜ  ልንገራችሁ፡፡ አባቶች ዘፍ.1፡1-4 ያለው ነቢዩ ሙሴ  ስለክርስትና በምሥጢር የተናገረባት ነው ብለው ይተረጉሙታል፡፡ “ቀንም ሆነ ሌሊትም ሆነ አንድ ቀን” የሚለውም ስምንተኛዋ ቀን ናት ይሏታል፡፡ ይህቺ ቀን ፀሐይና ጨረቃ እንዲሁም ከዋክብት ለምድር ብርሃንን ከመስጠታቸው በፊት የነበረች ቀን ነች፡፡
በእርግጥ እንዲህ ሲሉ አንዳች መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት ሳይዙ አይደለም፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ እንዲህ ይለናል “ በክርስቶስ ፊት የእግዚአብሔርን የክብሩን ብርሃን እንዲሰጥ በልባችን ውስጥ የበራ ፡- በጨለማ ብርሃን ይብራ ያለ እግዚአብሔር ነውና” (2ቆሮ.4፡6፤ዘፍ.1፡3) ይለናል።