Tuesday, March 24, 2015

ተወዳጆች ሆይ ጦሙ እንዴት ይዙአችኋል?

በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
15/07/2007

መቼም ጦምን ከጸሎት ጋር አስተባብሮ የያዘና ራሱን በእግዚአብሔር ፊት አቁሞ ስለ መተላለፉ በአምላኩ ፊት የሚያነባ ክርስቲያን የንስሐ እንባው የኃጢአት እድፉን ጠርጎ ስለሚያስወግድለት በሰዎች ላይ የማይፈርድ፥ እንደ ግብዝ ጦመኞች ልታይ ልታይ ማለት የሌለበት፥ ለሰው ልጅ ያለው ፍቅር የበዛለት፥ አንደበቱም ይሁን ልቡ ከጸሎትና ከልመና እንዲሁም ከምልጃ የማያርፍ ፥ ቃሉን ማንበብ የሚወድ፥ በቃሉ መመሰጥ የሆነለት፥ የራሱን እንጂ የሰዎችን ነውር ለማየት የማይፈቅድ፥ ስለራሱ ኃጢአት በአምላኩ ፊት በመንፈስ ሆኖ የሰማይን ፊት እንኳ ለማየት የማልበቃ ኃጢአተኛ ነኝ እያለ ደረቱን የሚደቃ ሰው መሆንን ገንዘቡ እንደሚያደርግ ሳይታለም የተፈታ ጉዳይ ነው።