Wednesday, April 8, 2015

የጌቴሴማኒው ጸሎት (ቅዱስ ኤፍሬም)



ትርጉም በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
30/07/2007

“ነፍሴ እስከሞት ድረስ እጅግ አዘነች” አለ የክብር ጌታ የሆነው ጌታችን፡፡ የተሰማውን እንዲህ ብሎ በግልጥ በመናገሩ የክብር ጌታ የሆነው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አላፈረም፡፡ ለማስመሰልም ብሎ አይደለም፤ በእውነት ነፍሱ እስከሞት ድረስ አጅግ ስላዘነች እንጂ፡፡ ምክንያቱም በእውነት የእኛን ደካማ የሆነ ሥጋችንን በመልበሱና የሥጋን መከራ ከምትካፈለው ነፍሳችን ጋር አንድ በመሆኑ ነው እንጂ፡፡ እርሱ የተናገረው በሙሉ እውነት ነው፤ እንደ አስመሳይ የሰወረን አንዳች ነገር የለም፡፡ በዚህም አንድ አማኝ በሕይወት ዘመኑ ሁሉ ራሱን እንዳያስታብይና እውነትን እንዳይሰወራት ጌታችን በተግባር አብነት ሆኖት እናገኘዋለን፡፡