Wednesday, November 28, 2012

በቤተክርስቲያን የሚታየው የሥላሴ መልክ



ትርጉም በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
19/03/2005

እያንዳንዱ ሰው በሦስትነቱ በሚመለከው እግዚአብሔር አርዓያና አምሳል እንደተፈጠረ ቤተክርስቲያን ደግሞ በሥላሴ ውስጥ ባለ ልዩነትና አንድነት አምሳል ልጆችን በመውለዱዋ ሥላሴን ትመስለዋለች፡፡ እግዚአብሔር ምንም በአካልና በግብር ሦስት ብንለውም አንድ እግዚአብሔር ብለን እንደምንጠራውና አካለቱም በየራሳቸው ሕልዋን እንደሆኑ ቤተክርስቲያንም እያንዳንዱ አማኝ ክርስቲያን በአንድ ክርስቶስ አካል አንድ ሲሆን አንዱ ካንዱ የሚለይበት የየራሱ አካል አለው፡፡ እግዚአብሔር በሦስነቱ ሳይነጣጠል በሰው ሰውነት ውስጥ እንዲያድር እንዲሁ የቤተክርስቲያን አባላት የሆኑ ሁሉ አንዱን የእግዚአብሔርን መንግሥት ይወርሳሉ፡፡ በቤተክርስቲያን ስልጣንና ነጻ ፈቃድን በተመለከተ ምንም ጠብ እንደሌለ ሁሉ ፍጹም አንድነትም አለ፡፡ በቤተክርስቲያን አንዱ ሁሉን ጠቅልሎ መያዝ ፈጽሞ የለም፡፡ እንደ ኦርቶዶክሳዊው አስተምህሮ “ቤተክርስቲያን ዓለማቀፋዊት ናት” ሲል ብዙሃን በልዩነታቸው አንድ የሚሆኑበትን በሥላሴ የሚታየውን ታላቅ የሆነውን ምሥጢር ታሳቢ በማድረግ ነው፡፡