Wednesday, February 12, 2020

ቀለማት በቤተ ክርስቲያን


ዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
04/06/2012 ዓ.ም
አዲስ አበባ
መዝሙረኛው ዳዊት፡- “ለእግዚአብሔር ምድር በምልዓ ምድርና ሞላዋ ለእግዚአብሔር ናት፥ ዓለምም በእርስዋም የሚኖሩ ሁሉእንዲል ለእግዚአብሔር ከፍጥረት ወገን የእርሱ ያልሆኑና ያለምክንያት የፈጠራቸው ፍጥረታት ከቶ ማግኘት አይቻልም፡፡ እርሱ በተለይ ለሰው ልጅ የእርሱ የሆነውን ከብር እንዲያው በከንቱ ሰጠው፡፡ ለእግዚአብሔር መገዛት፣ እግዚአብሔርን ማሰብ፣ እንደ መላእክትና እንደ ቅዱሳኖቹ የእርሱን ክብር ለማየት መናፈቅ ፖለቲካ አይደለም ወዳጆቼ፡፡ ፖለቲካም ከሆነ በእርሱ ሥር ሆኖ መኖር ለእርሱም መገዛት ከምንም በላይ ተመራጭ ነው፡፡ የእግዚአብሔር የሆነውንም መጠቀም ቢያስከብር እንጂ የሚያዋርድ አይደለም፡፡ ይልቅ የእርሱን ክብር ያውም አምላክ የሚከብርበትን የራሳቸው ሊያደርጉ የሚቋምጡ ግብረ ሰዶማውያን ይፈሩ እንጂ እኛስ እንደ ቅዱሳን መላእክትና ቅዱሳን ነፍሳት የእርሱን ከብር በታች በምድር በላይ በሰማይ ማየትን እንናፍቃለን፡፡ ይህን ክብሩንም ስንመገብ እንኖር ዘንድ ተጠርተናል፡፡