Monday, December 24, 2012

ወንድሞቼና እኅቶቼ በጋብቻ መነኩሳት ትሆኑ ዘንድ ምኞቴ ነው!!



በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
15/04/2005
ፍጹም አንድ መሆን፡፡ የራስን አካል የሚያውቁትን ያህል ማወቅ ምንኩስና የሚለውን ቃል ፍቺ ይሰጠናል፡፡ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ መንፈሳዊ ጋብቻ የሚለው በመለኮትና በሥጋ መካከል የተፈጸመውንና በልደት የተገለጠውን ተዋሕዶን ነው፡፡ ይህን ጋብቻ ይለዋል፡፡ አንድ ክርስቶስ፣ አንድ ኢየሱስ፣ አንድ የእግዚአብሔር ልጅ፣ እርሱ የመለኮትና የሥጋ ተዋሕዶ ውጤት ነው ይህን ለሰው ልጆች ካለው ፍቅር የተነሣ በገዛ ሥልጣኑ አደረገው ፡፡ ፍጹም የተዋሐዱ ፈጽሞ የማይለያዩ አንድ አካል ብቻ የሆነ፡፡ መነኮስ ማለትም አንድ ብቻ፤ ብቸኛ ማለት ነው፡፡ሁለቱ አንድ ይሆናሉ” የሚለው ቃል ሲፈጸም አንድብቸኞች ይሆናሉ ግን ሙሉ ናቸው፡