Thursday, May 31, 2012

‹‹አባታችን ሆይ››በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ(ክፍል ሁለት)


v በጸሎታችሁ አሕዛብን አትምሰሉአቸው
ትርጉም በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
23/09/2004
በመቀጠል ጸሎታቸንን እንዴት ማቅረብ እንዳለብን ያስተምረናል፡፡ ‹‹አሕዛብም በመናገራቸው ብዛት እንዲሰሙ ይመስላቸዋልና ስትጸልዩ እንደነርሱ በከንቱ አትድገሙ›› (ማቴ.፮᎓፯)አለ፡፡...
ጌታችን ከዚህ አስቀድሞ ጸሎትን በተመለከተ ደግሞ ደጋግሞ አስተምሮ ነበር፡፡ በዚህም ቦታ አስቀድሞ ጻፎችና ፈሪሳውያንን እንደወቀሳቸው ሁሉ ‹‹በከንቱ አትድገሙ›› በማለት አሕዛብን ወቀሳቸው፡፡ እንዲህ የሚያደርጉ ወገኖችንም አሳፈራቸው፡፡
ጌታችን በትምህርቱ የምንሳብባቸውንና እኛም ልንፈጽማቸው የምንጓጓላቸውን ነገሮች ጎጂነት ነቅሶ በማውጠት አስተማረን፡፡ ምክንያቱም እኛ ሰዎች ስንባል በውጫዊ ገጽታቸው አምረውና አሸብርቀው በሚታዩ ነገሮች በቀላሉ ስለምንሳብ፣ በውጭ ሲታዩ ጻድቃን የሚመስሉትን ግብዞችን  መስለን መመላለስን ስለምንመርጥ ነው፡፡