Thursday, July 26, 2012

Christian philosophy on women and men interaction.



By Shimelis Mergia
19/11/2004
The spiritual understanding has a power to adjust the ideologies of secular thoughts. Those how are guading in natural law live like animals. Spiritual understanding for them foolihness. But we Christian can see above this. Our undertanding is above natural laws. We understand any thing in the help of Holy Spirit who is the creator of all created beings. so our thinking can shape the secular thoughts which are focused on the natural law only.
 Women have more tendencies to spiritual things than men. Beside others, they want to learn spiritual things from men. Unless otherwise, if men are not learn them piritual things beside others, they may hate them suggesting as one of the fornicetors who desiring their flesh. 
Their eyes looking from down to top but we men are looking from to down.
 Or they pull us down to earthily things; we also pull up them to heavenly things. This is natural law. Then both of us become in medium. That is the correct place of human beings. Human being is mediator, to visible and invisible creation.
Do you see the gravity which planted by God in our nature? Anybody cannot be escaped from the gravity of earth, until he stops to live on earth. Such like things; we couldn’t escape from the gravity of that God planted inside our nature until we live on earth. We men and women are pulling each other to live in the medium life.

ቅዱስ ገብርኤል ሆይ እስቲ ልጠይቅህ!


በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
19/11/2004
ዛሬ የጌታችንንና የአፍቃሪያችንን የኢየሱስ ክርስቶስን መልክና ግርማ ለብሶ በብሉይ ኪዳን ለቅዱሳን መጽናናትን ይሰጥ የነበረውና(ዳን.10፡5-5 ከ ራእይ.1፡14-16 ካለው ጋር ያነጻጽሩ፤ እንዲሁም ሕዝ. 1፡26 ከ ዳን.8፡15፤9፡21፤10፡18 እንዲሁም 3፡25 ያነጻጽሩ)በሐዲስ ኪዳንም የድኅነት ብሥራትን ይዞ ወንድሞቻችንን መላእክትን ወክሎ እንዲሁም ነፍስን በደስታ በምታስጨንቅ ፍስሐ ተሞልቶ፣(ሉቃ፡15፡10) ወደ ድንግል በመምጣት ሕዝቡን ከኃጢአት የሚያድናቸው የስሙ ትርጓሜ መድኀኒት የሆነውን "ኢየሱስን በድንግልና ጸንሰሽ በድንግልና ትወልጃለሽ"(ሉቃ፡1፡31) ብሎ ያበሠረ የተወዳጁ መልአክ የቅዱስ ገብርኤል ክብረ በዓል ነው፡፡
 ሰውና አምላክ ፍጹም እርቅን የፈጸሙባትን ያቺን ዕለት ሳስባት ነፍሴ በሐሴት ትሰክራለች፡፡ ልጅ ከእናትና ከአባት ጥምረት ይወለዳል ፡፡ ስለዚህ ልጅ የእናትና የአባት ውሕደት አማናዊ መገለጫ ነው፡፡ እንዲሁ እግዚአብሔር አብ ለእኛ ያለውን ጥልቅ ፍቅር ሊገልጥልን ስለወደደ ልጁን እግዚአብሔር ወልድን ከድንግል በሥጋ ይወለድ ዘንድ ላከው፡፡  ልጁም ከእናታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሱዋ ነፍስ ነስቶ በመወለድ ፍጹም እርቅ በሰውና በእግዚአብሔር  መካከል መፈጸሙን በልደቱ አበሠረን፡፡ 
ከአባት አብራክና ከእናት መኀፀን የተወለደን ልጅ አካፍሎ ወደፊት ለአባትና ለእናት መስጠት እንዳይሞከር እንዲሁ እግዚአብሔር ወልድ ከእናታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም በሥጋ ከተወለደ በኋላ አምላክ ወሰብእ ተብሎ ይኖራል እንጂ ወደፊት ተከፍሎ የለበትም፡፡