Saturday, December 29, 2012

“እንዳይፈረድባችሁ አትፍረዱ” በቅዱስ ኤፍሬም



ትርጉም በዲ/ን ሽመልስ
20/04/2005
ቅዱስ ኤፍሬም “እንዳይፈረድባቸሁ አትፍረዱ” የሚለውን ኃይለ ቃል እንዲህ ይተረጉመዋል፡፡(ማቴ.7፡1-2) “ጌታችን አትፍረድ ሲል ኢፍትሐዊ ፍርድን ማለቱ ነው፡፡ ስለዚህም ኢፍሕታዊ ፍርድን ብትፈርድ ባንተ ላይ ይፈረድብሃል፡፡ በመሆኑም ፍርድን የሚለይ መንፈሱ ሳይኖርህ አትፍረድ፡፡ ፍትሐዊ መስሎህ ፍትሐዊ  ያልሆነ ፍርድን ልትፈርድ ትችላለህና፡፡ እንዲህም በማድረግህ ከፍርድ አታመልጥም፡፡
በመሆኑም ይህ ቃል “ለሰዎች ኃጢአታቸውን ይቅር ብትሉ  የሰማዩ አባታችሁ ይቅር ይላችኋልና”(ማቴ.6፡4) ከሚለው ኃይለ ቃል ጋር መጣመር አለበት፡፡ ይህ ኃይለ ቃል አትፍረድ ከሚለው ሕግ ጋር እንዴት ይጣመራል? ፍትሐዊ የሆነ ፍርድን በአንድ ሰው ላይ ስትፈርድ በጸጋው ሕግ ደግሞ ይቅር ልትለው ይገባሃል፡፡ ቅን የሆነ ፍርድን ፈርዶ በጸጋ ግን ይቅር ላለ ሰው እግዚአብሔር አምላክም ይቅር ይለዋል፡፡ ስለዚህ ጌታችን ቅን ፍርድን ምክንያት አድርገው ለበቀል ለሚነሳሱ ሰዎች  “እንዳይፈረድባችሁ አትፍረዱ” ብሎ አስተማረን፡፡ ይህም ማለት “ራሳችሁ አትበቀሉ” ማለቱ ነው፡፡ “በቀል የኔ ነው እኔ ብድራቱን እመልሳለሁ” እንዲል ጌታችን፡፡(ሮሜ.12፡19) ሌላው ደግሞ በመልክ ወይም ስለወደዳችሁ እንዳው በከንቱ አትፍረዱ ነገር ግን ከጥፋታቸው ይማሩ ዘንድ ምከሩዋቸው ገሥጾአቸው ሲለን ነው፡፡