Saturday, August 18, 2012

ደብረ ታቦር በቅዱስ ኤፍሬም



ትርጉም በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
12/12/2004
ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለሐዋርያት“እውነት እላችኋለሁ የሰው ልጅ በመንግሥቱ ሲመጣ እስኪያይ ድረስ ከዚህ ከሚቆሙት ሞትን የማይቀምሱ አንዳንዶች አሉ፡፡”(ማቴ.16፡28)የማለቱ ምክንያት በትንሣኤ እርሱን ለመቀበል በሕይወት የሚቆዩ እንዳሉ ሲያስረዳቸው ነው፡፡፡ ስለዚህም ጌታችን ሞትን ሳይቀምስ ከእርሱ ዘንድ የተነጠቀውን ኤልያስንና በእርሱ ሕያው የሆነውን ሙሴን ከመቃብር በማስነሣት ከሦስት ምስክሮች ጋር በደብረ ታቦር  ተራራ ላይ ግርማ መለኮቱን ገለጠልን፡፡ እነዚህ ሦስቱ አካላት ክርስቶስ ለሚመሠርታት መንግሥት(ቤተክርስቲያን) ምስክር የሚሆኑ  አዕማድ ናቸው፡፡(ቤተክርስቲያን ማለት በሥጋ ሞት የተለዩ የጻድቃን ነፍሳትና እንደ አልያስም ሞትን ያልቀመሱ ቅዱሳን እንዲሁም በምድር ሕያዋን ሆነን የምንኖር ክርስቲያኖች ኅብረት ማለት ናትና፡፡ ይህን  ምንም እንኳ በዐይናችን ለማየት ባንበቃም በእምነት ዐይኖቻችን  እንመለከተዋለን፡፡ በዚህም በደብረ ታቦር ተራራ ላይ ለሐዋርያት የተገለጠው መገለጥም ለዚህ እምነታችን  እውነተኛ መረጋገጫችን ነው፡፡)