Thursday, January 19, 2012

“በዓለ ጥምቀት የሙሽሪት ምዕመናን የደስታ ቀን”




ዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
10/05/2004
አምላክ ሆይ በነቢዩ ኢሳይያስ “ከነፍሱ ድካም ብርሃን ያያል ደስም ይለዋል ጻድቅ ባርያዬ በዕውቀቱ ብዙ ሰዎችን ያጸድቃል ኃጢአታቸውንም ይሸከማል፡፡”(ኢሳ.53፡11) ተብሎ አስቀድሞ የተናገረው እውን ሆኖ ዛሬ በዐይናችን ተመለከትነው፡፡ ጌታ ሆይ! በሕማምህ ወለድከን፤ በጥምቀትም ከሞትህ ጋር በመተባበር በመንፈስና በእሳት በመጠመቅ እሳታውያንና መንፈሳውያን የሆኑ መላእክትን መሰልናቸው፡፡ ስለዚህም በእደ ዮሐንስ በባሕረ ዮርዳኖስ በመጠመቅ ለእኛ ጥምቀትን የመሠረትክባት ይህቺን ዕለት በታላቅ መንፈሳዊ ደስታና ፍቅር እንዲሁም በታላቅ ተመስጦ ሆነን እናከብራታለን፡፡
ጌታ ሆይ ልጆችህ ልዩ ልዩ ሕብረ ቀላማት ባላቸው አልባሳት አጊጠውና ደምቀው ቅዱስ ሥጋህንና ክቡር ደምህን ከተቀበሉበት ማዕድህ፣ አምሳለ መስቀል ከሆነው ከምሕረት ቃል ኪዳን ታቦትህ ፊት ሆነው፣ በሐዋርያት ለአንተ ለሰማያዊው ሙሽራ የታጩበትን  ቀን ነፍስን በሐሴት በሚሞላ መንፈሳዊ ዝማሬና በታላቅ ደስታ ሆነው ሲያከብሩ ከላይ ከአርዓም ተመልከት፡፡

በእውን ሕፃናት አምላካቸውን አያውቁትምን?(ክፍል ሁለት)



ከዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
10/05/2004
ቅዱስ ኤፍሬም ጥምቀትን ነቢዩ ኤርምያስን በተሸከመች ማኅፀን መስሎ ሲያስተምር “ነቢዩ ኤርምያስ ገና ከእናቱ ማኅፀን ሳለ ተቀደሰ ተማረ፡፡ ደካማ የሆነችው ማኅፀን የፀነሰችውን ቀድሳ የወለደች ከሆነ እንዴት ጥምቀት ከእርሷ ማኅፀን የተፀነሱትን ይበልጥ ቀድሳና አስተምራ አትወል! ጥምቀት ተጠማቅያንን ንጹሐንና መንፈሳውያን አድርጋ ትወልዳቸዋለች” ይለናል፡፡ ከቅዱሱ አስተምህሮ  እንደምንረዳው ገና ከእናታቸው ማኅፀን ሕፃናት ፈጣሪያቸውን እንደሚያቁና እንደሚለዩ ነው፡፡  ይህን አስመልክቶ ቅዱስ ዳዊት "ኃጥአን ከማኅፀን ጀምረው ተለዩ ከሆድም ጀምረው ሳቱ፤ ሐሰትንም ተናገሩ"ይለናል(መዘዝ.56፡3) ቅዱስ ጳውሎስ ስለኤሳውና ስለያዕቆብ ሲናገር “ርብቃ ደግሞ ከአንዱ አባታችን ከይስሐቅ በፀነሰች ጊዜ ልጆቹ ገና ሳይወለዱ በጎ ወይም ክፉ ምንም ሳያደርጉ ከጠሪው እንጂ ከሥራ ሳይሆን በምርጫ የሚሆን የእግዚአብሔር አሳብ ይጸና ዘንድ ከእርሱዋ ፡- ታላቁ ለታናሹ ይገዛል ተባለላት፡፡ ያዕቆብን ወደድሁ ኤሳውን ጠላሁ ተብሎ እንደ ተጻፈ ነው”(ሮሜ.9፡10) ብሎ ጻፈልን፡፡

በእውን ሕፃናት እግዚአብሔርን አያውቁትምን ?



በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
10/05/2004 
ቅዱስ ዮሐንስ መጥምቅ ከእናቱ ማኅፀን ሳለ የጌታውን እናት ድምፅ በሰማ ጊዜ ፈጣሪው እርሱን በአካል ሊገኛኘው ሽቶ ወደ እርሱ መምጣቱን አስተዋለ ፡፡ ከደስታው ብዛት የተነሣ ዓለሙ በሆነው ማኅፀን ቦረቀ ዘለለ ፡፡ አስቀድሞ በእናቱና በአባቱ የቅድስና ሕይወት ምክንያት እርሱን በመንፈስ ሲጎበኘው የነበረው እግዚአብሔር ቃል ፣ የፈጠረውን ሥጋ ለብሶ ከእናቱ ጋር ወደ እርሱ እንደመጣ ሲረዳ ሊተረጎም በማይሞከር ደስታ ተሞላ ፡፡