ዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
23/02/2005

ንጉሥ ዳዊትም እንዲሁ ከልጅነቱ
ጀምሮ ልቡን የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ፣ አንደበቱን የመንፈሱ አገልጋይ በማድረጉ እንደ ልቤ ተባለ፡፡ ከእርሱም ዘር ክርስቶስ እንዲወለድ
“ዘርህን ለዘለዓለም አዘጋጃለሁ፤ ዙፋንህንም ለልጅ ልጅ እመሠርታለሁ፡፡”(መዝ.88፡4) እንዲሁም “ከወገብህ የሚወጣውን ዘርህን
ከአንተ በኋላ አስነሣለሁ መንግሥቱንም
አጸናለሁ፡፡ እርሱ ለስሜ ቤትን ይሠራል የመንግሥቱም ዙፋን ለዘለዓለም አጸናለሁ” አለው፡፡ ይህን ቅዱስ ዳዊት በመንፈስ አስተውሎ
“ጌታዬ ሆይ! እግዚአብሔር ሆይ ! እስከዚህ ያደረስኸኝ እኔ ማን ነኝ? ቤቴስ ምንድን ነው? ጌታዬ እግዚአብሔር ሆይ! ይህ በፊትህ
ጥቂት ነበረ፤ ስለባሪያህም ቤት ደግሞ ለሩቅ ዘመን ተናገርህ፤ ጌታዬ እግዚአብሔር ሆይ! ይህ የሰው ሕግ ነው፡፡(2ሳሙ.7፡12-4፤
18-19)
ብሎ ጌታውን አመሰገነ፡፡ በዚህ ቦታ ይህ “የሰው ሕግ ነው” ያለው “ክርስቶስን መምሰል” ነው፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ይህን ለማስረዳት "የሚያምኑ ሁሉ ይጸድቁ ዘንድ
ክርስቶስ የሕግ ፍጻሜ ነውና” ብሎ ጽፎልናል፡፡(ሮሜ.10፡4)