ትርጉም በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
15/09/2004
ከዕለታት በአንዱ ቀን ከወንድሞቼ
በስጦታ ዕንቁ ተቀበልኩኝ፤ በዚህ ዕንቁ ውስጥ ታላቅ የመንግሥቱን ምሥጢርንና የገዢው የክርስቶስን ምሳሌ ተመለከትኩ፡፡ ዕንቁ ለእኔ
ጥሩ የውኃ ምንጭ ሆነልኝ ፤ከዚህም ምንጭ የእግዚአብሔር ልጅን ምሥጢር ጠጥቼ ረካሁ፡፡
.jpg)
በዕንቁ ብሩህነት በባሕርይው ምንም ጨለማ የሌለበትን የእግዚአብሔር
አብ ብቸኛ ልጁን ተመለከትኩ፡፡ በእርሱም ውስጥ ግሩም የሆነውም ንጽሕናውን አስተዋለኩኝ፤ ከእኛም የነሣውንም ሥጋ ቅድስናውንና ንጽሕናውን
ተረዳሁ፡፡ በዚህ ዕንቁ ውስጥ ያየውትን ያለመከፈል አንድ የሆነውን የሥጋንና የመለኮትን ተዋሕዶ ተመለከትኩ፡፡
በዕንቁው ውስጥ እንዲሁ የእርሱን ንጹሕ የሆነውን ፅንሰት አስተዋልኩ፡፡
ቤተ ክርስቲያን በምትሰኘው ቅድስት ድንግል ማርያም ማኅፀን የተፈጸመውን የእግዚአብሔር ልጅ ፅንሰትን ተረዳሁ፡፡ እርሱዋ እርሱን
የተሸከመችው ደመናው ናት፡፡ የእርሱዋም ምሳሌ ሰማይ ነው፡፡ ከእርሱዋም የጽድቅ ፀሐይ በመውጣት ለዓለም አበራ፡፡