Labels
- ለቤተ መጻሕፍቶዎ (2)
- ምልከታዎቼ (45)
- ቅንጭብጭብ (22)
- ተግሣጻትና ጸሎታት (26)
- ኦርቶዶክሳዊ ጽንሰ ሃሳቦች (78)
- ከቅዱሳን አባቶች ማዕድ (41)
- ኪን መንፈሳዊ (20)
- የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብና ከንባቡ ለወጡ ጥያቄዎች የተሰጡ መልሶች (6)
Saturday, February 18, 2012
ጦምን አስመልክቶ የቅዱሳን አባቶች አስተምህሮ
በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
10/06/2004
“በጦም ወቅት አንድ ክርስቲያን በፈቃደኝነት አንድ በጎ ሥራን ጎን ለጎን ቢፈጽም መልካም ነው፡፡ ነገር ግን ከሰዎች ምስጋናን ወይም አንዳችን
ነገር ሽቶ የሚጦም ከሆነ ግን ጦሙ በእግዚአብሔር ዘንድ የማይወደድ ጦም ይሆንበታል፡፡ ማንኛውም በጎ ሥራ ስንሠራ ለእግዚአብሔር አምላካችን ካለን ፍቅር የመነጨ ይሁን፡፡
እንዲያ ካልሆነ ግን እግዚአብሔርን ደስ ልናሰኝ አይቻለንም፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስን ጌታችን በመንጎቹ ላይ ሲሾመው ለእርሱ ያለውን ፍቅር
ተመልከቶ ነበር፡፡ እግዚአብሔርን የሚያፈቅር ሰው የሚፈጽማቸው የትኞቹም በጎ ምግባራት በእግዚአብሔር ዘንድ የተወደዱለት ይሆኑለታል፡፡
ፍጹማንም ናቸው፡፡ ስለዚህም ማንኛውንም በጎ ሥራዎቻችንን ስንሠራ እርሱን በማፍቀር ላይ የተመሠረተ ይሁን፡፡”
“አንድ ሰው ምንም እንኳ መላ የሕይወት ዘመኑን በትህርምት ሕይወት
መምራት ያለበት ቢሆንም በዚህ በዐቢይ ጦም ግን ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ኃጢአቱን ለካህን ተናዝዞ ለድሆች ምጽዋትን በማድረግ በአግባቡ ሊጦም ይገባዋል፡፡ እነዚህን
ዐርባ የጦም ቀናት በአግባቡ በጎ ሥራዎች አክለንባቸው የጦምናቸው እንደሆነ ቸሩ ፈጣሪያችን ዓመት ሙሉ ባለማወቅ የፈጸምናቸውን ኃጢአቶቻችንን
ይደመስስልናል፡፡ (ዮሐንስ አፈወርቅ )
"በአረጀ አቁማዳ አዲስ የወይን ጠጅ የሚያኖር የለም"(ካለፈው የቀጠለ)
በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
10/06/2004
ይህ እንዲሆንም ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ራሱን ስለመንጎቹ በመስቀል ላይ ሠዋ፡፡ ሙሽሪት ምዕመናንንም
በደሙ ገዛት፡፡ ከጎኑ በፈሰሰው ውኃ አንጽቶ ከጎኑ በፈሰሰውም ደሙ ቀድሶ የራሱ አደረጋት፡፡ እንዲያም ስለሆነ ለሰማያዊው ንጉሥ
ሰማያዊት ሙሽራው ሆነችው፡፡ ሙሽሪት የተባልነው እኛ ነን፡፡ አሁን እኛ በክርስቶስ አምላክነት አምነን በሥላሴ ስም የተጠመቅን ክርስቲያኖች
በመንፈስ ቅዱስ የታደሰ ሰማያዊ ሰብእናን ገንዘባችን በማድረጋችን የእግዚአብሔር ልጆች ተሰኝተናል፡፡ስለዚህም የእግዚአብሔርን ጥልቅ
የሆነ አሳብን እንኳ በመንፈስ ቅዱስ ታግዘን ለመረዳት እንችላለን፡፡ እንደ መንፈስ ቅዱስም ፈቃድ በመመላለስ ሰይጣንን ድል የምንነሣበትን
የጽድቅ ጥሩርን ለብሰናል፡፡

Subscribe to:
Posts (Atom)