Saturday, May 25, 2013

አቤቱ ይህን አትንሣን!!!



17/09/2005
በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
ሰው የሚድነው በእግዚአብሔር ጸጋ ነው “በጸጋ ድናችኋልና” እንዲል፡፡ ክርስቶስ ዘለዓለማዊውን ጸጋውን ከሰጠን ቆየ ክርስትናም በክርስቶስ ከተመሠረተች እጅግ ቆየች ግን አሁንም ያው ነች ሰማያዊት ናትና የዘመን ቁጥር የላትም ሁሌም አዲስ ናት፡፡ ሰዎችን ዘመን ከማይቆጠርባት ሰማያዊት ሀገር ታፈልሳለች በዚያም ሰማያውያን ቅዱሳን መላእክትና ቅዱሳን ነፍሳት ከትመዋል፡፡ ሰው ልቡናው ከበራ የሚኖርባትን ዘመን የማይቆጠርላትን ሰማያዊቱን ዓለም ይረዳታል ጣዕሙዋንም ይቀምሳል፡፡ ጣዕሟን ማንም በቃላት ሊገልጣት አይችልም፡፡ ለዚህ ዓለም ቋንቋ ባዕድ ናት ሕይወቱዋም ልዩ ነው፡፡ ይህችን ጣዕም እየቀመሱ መኖር እንዴት መታደል ነው!!! ቢሆንም የሚወደን አምላክ እርሱዋን አልነሣንም ግቡም ይህ ነው የዚህች ሰማያዊት ስፍራን ጣዕም በሁለመናችን እንረዳትና በእርሱዋ ውስጥ ለዘለዓለም እንድንኖር ነው፡፡ ጌታ ሆይ ከዚህች ሥፍራ በመንፈስ እንዳንወጣ ሁሌም የዚህችን ሰማያዊት ሥፍራ እያጣጣምን እንድንኖር እርዳን ለዘለዓለሙ አሜን፡፡ 

1 comment:

  1. Kalehywet Ysemalen Mengesetesemayten Ywerselne Ymengesetu Werashe Ysemu Kedashe Ydergelen Amen

    ReplyDelete