Friday, January 20, 2012

ክርስቶስ ለእኛ ኦርቶዶክሳዊያን ማን ነው?



በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
12/05/2004 
እርሱ የእግዚአብሔር በግ ነው፤ እርሱም መሥዋዕት ነው፤
እርሱ ስለብዙዎች ኃጢአት የተሠዋው ፍሪዳ ነው፤ እርሱ መሥዋዕቱን የሚያቀርብ ሊቀ ካህናት ነው፤መሥዋት ተቀባዩም እርሱ ነው፤
ስለእኛ መከራን የተቀበለው እርሱ ነው፤ ስለእኛም የራራልን እርሱ ነው፤
እርሱ ሙሽራ ነው ፤እርሱ ራሱ ሙሽሪትም ነው፡፡(ከእናታችን የነሣው ሥጋ ለጌታችን እንደሙሽሪት ነው፡፡ ይህ ሥጋ ግን አምላክ በመሆኑ ሙሽራ ሆነ፤ በሐዋርያትም እኛ ለእርሱ ታጨን፡፡ ስለዚህም እርሱ ሙሽራ ነው፤ እርሱ ራሱ ሙሽሪት ነው አልን)
እርሱ  የሰርጉ ቤት ነው፤ እርሱ ራሱ  የሰርግ ቤቱ አሳላፊ ነው፤
እርሱ ገነት ነው፤ እርሱ ራሱ የሕይወት ዛፍ ነው፤
እርሱ  ሰማያዊቱ ኢየሩሳሌም ነው፤ እርሱ ራሱ መቅደሳችንና ቅድስተ ቅዱሳናችን ነው
በውኆች የተመሰለው እርሱ ነው፤ እርሱ ራሱ እኛ የምንኖርበት ዓለማችን ነው፤
እርሱ  ምግባችን ነው፤ እርሱ ራሱ ስለድኅነታችን የሚመግበን መጋቢያችን ነው፤
እርሱ ሕያው የሆነው ሕብስት ነው፤ እርሱ የሕይወት ውኃችን ነው፤
እርሱ እውነተኛው የወይን ግንድ ነው፤ እርሱ ራሱ የደስታ ወይናችን ነው፤
እርሱ ዕንቁዋችን ነው፤ እርሱ ራሱ መዛግብታችን ነው፤
እርሱ መረባችን ነው፤ እርሱ ራሱ ተዋጊያችን ነው፤
እርሱ የጦር መሣሪያችን ነው፤ እርሱ ሁሉን ድል የሚነሣ ነው፤
እርሱ ግዝረታችን ነው፤ እርሱ ራሱ ሰንበታችንና ሕጋችን ነው፤
እርሱ የቅዱሳን ኅብረት ለሆነችው ቤተክርስቲያን ራስ ነው፤ እርሱ መልካሙ የስንዴ ቅንጣት ነው፤
እርሱ የወይን እርሻችን ነው፤ የእርሻውም ባለቤት እርሱ ነው፤
እርሱ ግርማችን ነው፤ እርሱ እምነታችን ነው፤
እርሱ ሰርጋችን ነው፤ እርሱ የሰርግ ልብሳችን ነው፤
እርሱ የሕይወት መንገዳችን ነው፤ እርሱ በራችን ነው፤
እርሱ የጽድቅ ፀሐያችን ነው፤ እርሱ የነፍሳችን ብርሃን ነው፤
እርሱ ሕይወት ነው፤ እርሱ መንግሥተ ሰማያት ነው፤
እርሱ መጀመሪያ የሌለው መጀመሪያ፣ መጨረሻ የሌለው መጨረሻ፣ አልፋና ኦሜጋ ነው፤
ስለዚህም እኛ ኦርቶዶክሳዊያን በክርስቶስ ከክርስቶስ ለክርስቶስ የሆንን የክርስቶስ ነን!!!

1 comment:

  1. ወንድሜ ጥሩ ብለሃል፡፡ ለኛ ለኦርቶዶክሳዊያን ብቻ ሳይሆን በክርሰቶስ ኢየሱስ ክርስቲያን ለተባሉት ሁሉ ክርስቶስ ከተባለለት በላይ ነው፡፡ ግን ፍርሃት አለኝ፡፡ እውነት የኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ክርስቶስን እንደማወቋ ታምነዋለች? ማወቅና ማመን ይለያያልና፡፡ በኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ከክርስቶስ ይልቅ የጻድቃንና የመላዕክት ክብር ገኖ ይታያል፡፡ በብዙ ነገር ክርስቶስን ሸፍነነዋል፡፡ እንደዕውቀታችን አላመነውም፡፡ በማወቅ ላይ የተመሰረት እምነት መልካም ነበር፡፡ ነገር ግን አልተጠቀምንበትም፡፡ እግዚአብሔር አምላክ አይኖቻችንን ያብራልን፡፡ ብርሃን ይሁን ይበል!!!!

    ReplyDelete