Tuesday, July 31, 2012

St. Epherm said about us



By Shimelis mergia.
25/11/2004

“The King’s Son,(Jesus Christ) when he saw her wickedness came and betrothed to Himself the church(that means we are) … whose love and truthiness He had tested, He made her one with Himself, that there might be not separation. See, she sits in the King’s palace, dressed in the ornaments of the King. The month Nisan serves her,(the crucifixion of Him on the Cross) arrayed and adorned with flowers. Glory to You, Lord of Nisan (Passover "
ፋሲካ”)"
But now we men, when we saw the women who adorned with the glory of King and sat on the palace of glory, we desire them to be our wives, who by whom sanctified and cleansed and washed with Water and Word, and made them without spot and wrinkle. We felt by the beauty of their holiness and Glory. So we asked our beloved God like our former father Adam, to give them to us as wives like this:- “This is now bone of my bones, and flesh of my flesh; she shall be called Woman, because she was taken out of Man (the Second Adam Christ)” Oh what amazing mystery is it Oh men !!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!!! Gory to you oh God, Glory to the women who adorning themselves with true Christianity!!!
የንጉሥ ልጅ የሆነው እርሱ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የእርሷን መተላለፍ ተመልክቶ ቤተ ክርስቲያንን የራሱ ትሆን ዘንድ አጫት፡፡(ቤተ ክርስቲያንም የተሰኘነው እኛ ነን) የእርሷን ለእርሱ ያላትን ፍቅርና ታማኝነት ፈትኖ ከእርሱ አካል ጋር አዋሐዳት፡፡ ይህች ቤተ ክርስቲያን በንጉሥ ጌጣጌጦች ተውባ ከንጉሥ ቤተ መንግሥት መቀመጫዋን እንዳደረገች አስተውል፤ የኒሣ ወርም ታገለግላታለች፡፡( በመስቀሉ የሰጣት ምሥጢራት እርስዋን ያገለግሏታል)(ቅዱስ ኤፍሬም)
(እኔ ደግሞ ይህን አልኩበት ታቸችያለወውን ጨርከኩበት) 

እኛ ወንዶችም በንጉሥ ክርስቶስ አጊጠውና  ከንጉሥ ቤተ መንግሥት ከብረው የተገኙትን በመስቀሉ በፈጸመው ቤዛነት በቃሉና በተቀደሰው ውኃ ንጹሕ ያደረጋቸውን ሴቶች ስንመለከት የእኛ ሚስቶች የሆኑ ዘንድ ተመኘን፡፡  በእነርሱ ቅድስናና ግርማ ተማርከን ወደቅን፡፡ ስለዚህ ሰውን ወዳጅ የሆነውን እግዚአብሔርን እንደ ቀድሞው አዳም “እነዚህ ሴቶች ከሥጋችን ሥጋ ከአጥንታችን አጥንት ናቸውና በዚህም ምክንያት ሴቶች ተብለዋል፡፡ ምክንያቱም እነዚህ ሴቶች ከዳግማዊው አዳም ክርስቶስ የተገኙ ናቸውና፡፡ እናንት ወንዶች ሆይ ይህ ምሥጢር ምን የሚደንቅ! አምላካችን ሆይ ለዚህ ድንቅ ሥራህ ምስጋና  ይገባሃል፤ በእውነተኛ ክርስትና ራሳቸውን ያስጌጡ ሴቶችም ምስጋና ይገባቸዋል ለዘለዓለም በእውነት፡፡
 
 

Saturday, July 28, 2012

“ሽሽታችሁ በክረምት ወይም በሰንበት አይሁን”(በቅዱስ ኤፍሬም)የመጨረሻ ክፍል



ትርጉም በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
22/11/2004 ዓ.ም
ጌታችን “በሰገነት ላይ ያለ ወደ ኋላ አይመለስ”(ሉቃ.17፡31) በሚለው ኃይለ ቃሉ በእነርሱ ላይ ቁጣው ምንም የነደደ ቢሆንም የእነርሱን ጥፋት እንደማይወድ ያሳየበት ኃይለ ቃል ነው፡፡ “በዚያችም ወራት ለርጉዞች ለሚያጠቡ ወዮላቸው”(ማቴ.24፡19) ሲልም በጊዜው ስለፀነሱት ሴቶች ልጆቻቸው እየተናገረ ሳይሆን በሮማዊያን ጭንቅ የሆነ መከራን ትቀበላላችሁ ሲላቸው ነበር፡፡ ስለዚህም “ችግር በምድር ላይ በዚህም ሕዝብ ላይ ይሆናል”(ሉቃ.21፡23)ብሎ ተናገረ፡፡ በዚህም ምክንያት “ሽሽታችሁ በክረምት ወይም በሰንበት እንዳይሆን ጸልዩ” በማለት ከዚህ መከራ እንዲድኑ ጌታችን አስጠነቀቃቸው፡፡ እንዲህም ሲል የጽድቅን ሥራ የማትሠሩባት ቀን ትመጣለች፡፡ በዚያች ዕለት መብራታችሁን ከዘይታችሁ ጋር ሳትይዙ እንዳትገኙ፤ ይህም ማለት ፍቅርን ከምጽዋትና ከንጽሕና ጋር ወይም እምነትን ከምግባር ጋር ሳትይዙ እንዳትገኙ ተጠንቀቁ በዚያች በመጨረሻዋ ሰዓት ለመብራታችን ዘይት እንፈልግ በማለት ያም ማለት የትሩፋት ሥራዎችን እንሥራ ብትሉ አይቻላችሁም፤ ምክንያቱም ጊዜው የሥራ ሳይሆን የፍርድ ጊዜ ነውና፡፡(ማቴ.25፡1-13) ስለዚህም ጽድቅን ሳትሠሩ ጊዜው ፈጥኖ እንዳይደርስባችሁና እንዳይፈረድባችሁ በጸሎት ትጉ ሲል “ሽሽታችሁ በክረምት ወይም በሰንበት እንዳይሆን ተጠንቀቁ” አላቸው፡፡ በክረምት ፍሬ እንደሌለ በሰንበትም ሥራ የለም፡፡ ስለዚህም ሽሽታችሁ በክረምት ወይም በሰንበት አይሁን ሲል እምነትንና ምግባርን ሳትይዙ ድንገት ምጽአቱ እንዳይደርስባችሁ በጸሎት ትጉ ሲል ነው፡፡

“ሽሽታችሁ በክረምት ወይም በሰንበት አይሁን”(ትርጉም በቅዱስ ኤፍሬም)



ትርጉም በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
21/11/2004 ዓ.ም
ተወዳጆች ሆይ ዛሬ ጌታችን “እንግዲህ በነቢዩ በዳንኤል የተባለውን የጥፋት ርኩሰት በተቀደሰችው ሥፍራ ቆሞ ስታዩ አንባቢው ያስተውል”(ማቴ.24፡15) የሚለውን ኃይለ ቃል ትርጉም እንማማራለን፡፡ እንደሚታወቀው ኢየሩሳሌም ብዙ ጊዜ ጠፍታ በተደጋጋሚ መልሳ የተገነባች ከተማ ናት፡፡  ነገር ግን ይህ የትንቢት ቃል በኢየሩሳሌም የአምልኮው ሥርዐቱና በሌዋውያን ካህናት የሚቀርበው መሥዋዕት ፈጽሞ እንደሚቋረጥ የሚያስረዳ ኃይለ ቃል ነው፡፡ አስቀድሞ በነቢዩ ዳንኤል “የጥፋት ርኩሰት” የተባለውን አንዳንድ ተርጓሚያን  “ሮማውያን በቤተመቅደሱ እሪያ በመሠዋት ጭንቅላቱን ይዘው ወደ ቅድስተ ቅዱሳኑ እንደሚገቡና መቅደሱን እንደሚያረክሱት፤ ይህ በተፈጸመ ጊዜ የኢየሩሳሌም ጥፋት እንደቀረበ አንባቢው ያስተውል ሲል ነው ብለው ይተረጉሙታል፡፡(ፍጻሜው ግን ቅዱስ ጳውሎስ “እኔ እግዚአብሔር ነኝ ብሎ አዋጅ እየነገረ በእግዚአብሔር ቤተመቅደስ እስኪቀመጥ ድረስ አምላክ ከተባለው ሁሉ ሰዎችም ከሚያመልኩት ሁሉ በላይ ራሱን ከፍ ከፍ የሚያደርገው ተቃዋሚ እርሱ ነው” ብሎ የተናገረለት የሐሳዊው መሲህ መገለጥ ነው፡፡(2ተሰ.1፡4)