Tuesday, August 7, 2012

የቅድስት ድንግል ማርያም ዘለዓለማዊ ድንግልና



በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
2/12/2004
(1996 ዓ.ም ለሰንበት ትምህርት ቤት ማስተማሪያ የተዘጋጀ)
መጽሐፍ ቅዱስና ሌሎች የቤተ ክርስቲያን አባቶች ቅድስት ድንግል ማርያም ዘለዓለማዊ ድንግል እንደሆነች አስረግጠው ይስተምራሉ፡፡ እርሱዋ ቅድመ ወሊድ፣ ጊዜ ወሊድ፣ ድኅረ ወሊድ ድንግል ናት ፤ ሃሳቡዋም ሰውነቱዋን ለእግዚአብሔር አምላኩዋ ቀድሳ በድንግል መኖር ነበር፡፡ ይህን ከንግግሩዋ ማረጋገጥ ይቻላል፡፡ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ለቅድስት ድንግል ማርያም “ ደስ ይበልሽ ጸጋን የሞላብሽ ሆይ ጌታ ከአንቺ ጋር ነው፡፡… ማርያም ሆይ በእግዚአብሔር ፊት ጸጋን አግኝተሻልና አትፍሪ እነሆ ትጸንሻለሽ ወንድ ልጅም ትወልጃለሽ ስሙንም ኢየሱስ ትይዋለሽ…” ባላት ጊዜ የሷ መልስ “ወንድ ስለማላውቅ ይህ እንዴት ይሆናል” ነበር፡፡/ሉቃ. 1፥27-36/ ይህም በድንግልና ለመኖር እንደ ቆረጠች ያስረዳናል፡፡ አግብታ ልጅ የመውለድ ፈቃዱ ቢኖራት ኖሮ መልአኩን ከማን? ብላ በጠየቀችው ነበር፡፡ በተጨማሪም ወንድ ስለማላውቅ ማለቷ ወደፊትም ወንድ ባለማወቅ በድንግልና ለመኖር ለእግዚአብሔር ስለተሳልኩ እንዴት ይሆናል? ማለቷ ነበር፡፡

Sunday, August 5, 2012

ሐመረ ኖህ(በቅዱስ ኤፍሬም)



ትርጉም በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
29/11/2004
ቅዱስ ኤፍሬም በዚህ ቅኔያዊ ድርሰቱ ኖህ ከጥፋት ውኃ የዳነባትን መርከብ በቤተክርስቲያንና በመስቀሉ እንዲሁም በእምነት መስሎ ድንቅ በሆነ መልኩ አቅርቦት እንመለከታለን፡፡   
የኖህ ተምሳሌትነት በዘመኑ ከነበሩት ሕዝቦች ጋር ሲነጻጸር እንዴት ታላቅ ነበር፤ንጽሕናን እንደጥሩር ከለበሰው ኖህ ጋር በፍትሕ ሚዛን ሲመዘኑ እንደማይጠቅሙ እንደማይረቡ ሆነው ተቆጠሩ፡፡ፈጽሞ የማይነጻጸሩ ነበሩና በጥፋት ውኃው ሥር ዘቅጠው ቀሩ፡፡የኖህን ንጽሕና ከፍታ ለማሳየትም ኖህ በመርከብ ሆኖ ወደ ላይ ከፍ ከፍ አለ፡፡ በኖህ ንጽሕና ደስ ለተሰኘህ ለአንተ ለእግዚብሔር ክብር ይሁን፤ ለገዢነትህም ምስጋና ይገባል፡፡

Wednesday, August 1, 2012

For hypocrites


By Shimelis Mergia
25/11/2004

"You hypocrites cleanse first that which is within the cup and platter,(like our Mom Mary who sanctified her body for the dwelling place of the true Wine Jesus Christ, if you follow her footstep,) the outside of you may be clean also.(Matt.23:26)She cleansed her inner soul and body, sothat, God the Word came and dwelt and born to her. because of this, she open her lips with praise "ነፍሴ ጌታን ታከብረዋለች መንፈሴም በአምላኬ በመድኀኒቴ ሐሴትን ታደርጋለች…. እነሆም ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ይሉኛል ብርቱ የሆነ እርሱ በእኔ ታላቅ ነገርን አድርጎአልና ስሙም ቅዱስ ነው”