Sunday, June 3, 2012

ጦማችንና ምጽዋታችን ምን ይምሰል? በቅዱስ ኤፍሬም



ርጉም በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
26/09/2004
መግቢያ
ለቅዱስ ኤፍሬምና ለሌሎችም የሶርያ ቅዱሳን አባቶች ጦም፣ ጸሎት እንዲሁም ምጽዋት ለነፍስ እንደ ብርሃን ናቸው፡፡ ዐይን ያለ ብርሃን ድጋፍ እንደማታይ እንዲሁ ነፍስም ያለእነዚህ ድጋፍ መንፈሳዊውን ዓለም መረዳት አትችልም፡፡ ጌታችንም “እንግዲህ ዐይንህ ጤናማ ብትሆን ሰውነትህ ብሩህ ይሆናል፡፡ ዐይንህ ግን ታማሚ ብትሆን ሰውነትህ ሁሉ የጨለመ ይሆናል፡፡ እንግዲህ በአንተ ያለው ብርሃን ጨለማ ከሆነ ጨለማውስ እንዴት ይበረታ!”(ማቴ.6፡22)በማለት ብርሃን ያላቸው እነዚህን ነው፡፡ እነዚህን በአግባቡና ከከንቱ ውዳሴ ተጠብቀን የፈጸመናቸው ከሆነ መንፈሳዊ ማስተዋላችን እጅግ የጠለቀ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ ነገር ግን እነዚህን ከሰው ክብርን በመሻት የፈጸምናቸው ከሆነ እነዚሁ ራሳቸው መልሰው ያጠፉናል፡፡
እነዚህ በአግባቡ ካልተገለገልንባቸው በኃጢአትችን ላይ ኃጢአትን እንድንጨምር ያደርጉናል፡፡ ስለዚህ በእኛ ያለው ብርሃን (ጦም፣ጸሎት፤ እንዲሁም ምጽዋት) በከንቱ ውዳሴና በሌሎችም ኃጢአት ጨለማ ከሆነ በፊት ከፈጸምናቸው ኃጢአት ጋር ተደምረው እኛን ወደ ጥልቁ ጨለማ ይጥሉናል፡፡ ስለዚህም ነው ጌታችን “ በአንተ ያለው ብርሃን ጨለማ ከሆነ ጨለማውስ እንዴት ይበረታ” ማለቱ፡፡ ይህን ድንቅ የሆነ አስተምህሮ እንድታስተውሉትና እኔ በትርጉሙ እንደተደነቅሁ በእናንተም ትደነቁ ዘንድ ቅዱስ ኤፍሬም ወንጌላትን ከተረጎመበት መጽሐፉ ያገኘሁትን ትርጓሜ እነሆ ብያችኋለሁ፡፡ በዚህ አጋጣሚ መጽሐፉን ገዝቶ በመላክ የተባበረኝን ወንደሜን ሙሉጌታ ሙላቱን ከልቤ ላመሰግነው እወዳለሁ፡፡   
ጌታችን ጦማችን ምን መምሰል እንዳለበት ሲያስተምር “እንደ ጦመኛ እንዳትታይ ራስህን ተቀባ ፊትህንም ታጠብ በስውር የሚያይ አባትህም በግልጥ ይከፍልሃል” አለን፡፡(ማቴ.6፡18)

Saturday, June 2, 2012

THE ASCETICAL TEACHING IN THE WRITINGS OF ST. EPHREM



By Shimelis Mergia
From senior essay
25/09/2004
The Ascetical teaching of St. Ephrem was just like St. Paul teaching to the Corinthian Christians, who taught about virginity.(1cor.7:11) such Ascetical life which introduced by St. Paul and later by St. Ephrem  is more biblical than Egyptian monasticism. St. Paul taught about virginity like this;
 “I say this concession, not as a command. I wish that all men were as I am but each man has his own gift from God; one has this gift anther has that. Now to the unmarried and the widows I say: it is good for them to stay unmarried” (1cor.7:6-8)
 According to St. Paul virginity is the preferable way of life to please God. But he couldn’t say marital life cannot be pleased God. However, it may have obstacles to serve God in whole life.

Friday, June 1, 2012

"አባታችን ሆይ"በቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ (ክፍል ሦስት)


‹‹መንግሥትህ ትምጣ››
ትርጉም በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
25/09/2009
ይህም በጎ ሕሊና ያለው ሰው ጸሎት ነው፡፡ እንዲህ ዐይነት ሰው በዐይን በሚታዩ ምድራዊ ነገሮች የሚማረክ ሰው አይደለም፡፡ ወይም ይህን የሚታየውን ዓለም እንደ ትልቅ ቁምነገር የሚቆጥረው ሰው አይደለም፡፡ ነገር ግን ወደ አባታችን በጸሎት ይፋጠናል፡፡ከእግዚአብሔር ዘንድ የምትሰጠውንም መንግሥት ይናፍቃል፡፡ ይህ ፈቃድ ከመልካምና ከምድራዊ አመለካከት የተለየ ሕሊና ካለው ሰው ዘንድ የሚገኝ ነው፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ይህንን ሕይወት ዘወትር ይናፍቀው ነበር፡፡ ስለዚህም‹‹… የመንፈሱ በኩራት ያለን ራሳችን ደግሞ የሰውነታችን ቤዛ የሆነውን ልጅነት እየተጠባበቅን ራሳችን በውስጣችን እንቃትታለን››(ሮሜ.፰፡፳፫ )ብሏል፡፡ እንዲህ ዐይነት ናፍቆት ያለው ሰው በዚህ ምድር ባገኛቸው መልካም ነገሮች ራሱን አያስታብይም ወይንም በጽኑ መከራ ውስጥ ቢሆንም ከመከራው ጽናት የተነሣ አይመረርም ፡፡ ነገር ግን ወደ ሰማይ ወደ እረፍቱ ቦታ እንደገባ ሰው ምስቅልቅል ከሆነው ከዚህ ዓለም ሕይወት ነፃ የወጣ ሰውን ይመስላል፡፡