Sunday, January 22, 2012

ክርስቲያን ሆይ ይህን ልብ በል!!(ከአብርሃም ሶርያዊ)


ትርጉም በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
13/05/2004
ወገኔ ሆይ አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ፣ የእግዚአብሔር ወዳጆች ለተባሉት ወንድም/እኅት/ ፣ ከሐዋርያትና ከሰማዓታት ጋር ከበዛው ጸጋቸው ተካፋይ ፣ ከእርሱም ምስክሮች ጋር አንድ ማዕድን የምትካፈል ፣ የቅዱሳን ርስት ወራሽና ቅን በሆነው ፍርዱ ደስ ይልህ ዘንድ ከነቢያት የፍርድ ወንበር ላይ የተቀመጥክ ፣ ከቅዱሳን መላእክት ጋር በምስጋና የምትሳተፍ ፣ ከሱራፌልም ጋር የምትነጋገር ፣ ከኪሩበል ጋር በሰማያዊ ዙፋን ላይ የተቀመጥክ ፣ ከክርስቶስ የጸጋ ስጦታ ተካፋይ የሆንክ ፣ የብቸኛ ልጁ ሰርግ ታዳሚ ትሆን ዘንድ የተጠራህ ፣ የሰማያውያን ሠራዊተ መላእክት ወዳጅ ፣ የሰማያዊቱ ኢየሩሳሌም ዜግነት ያለህ ነህ ፡፡ አእምሮህ ውስጥ እነዚህ በክርስቶስ ለአንተ የተሰጡት የእግዚአብሔር ቸርነቶች ከተቀመጡ የጨለማው ዓለም ገዢ አገልጋዮች የሆኑ አንተን ሊያሰነካክሉህ አይችሉም ፡፡ በንስሐ ጽና ፡፡ ሕሊናን ከሚያቆሽሹ ከንቱ አስተሳሰቦች ራስህን ንጹሕ አድርግ ፡፡ ከእነዚህ ፈጽመህ ራቅ ከንቱ በሆኑ አስተሳሰቦችም አትሸበር፡፡”

No comments:

Post a Comment