Thursday, April 19, 2012

እናት



በወንድም ሸዋዓለም ፈቃዱ
12/08/2004

መነሻ ዳርቻ ፍጻሜ የሌለው፤
ጥንቱን የማላውቀው ፍጹም የማለየው፤
አለ አንዳች ስበት ከስሜት የጸዳ፤
ከእናት ያጣበቀ ከእናት የተቀዳ፡፡
እማዬ ፡- ያኔ… ያ…ኔ ክፉውን ከደጉ ያለየሁኝ ለታ፤
በቅጽበት ዐይን ያልተለየኝ ላፍታ፤
ከጡቶችሽ ምጌ ከልቤ ያኖርኩት፤
አንዳች ምሥጢር አለ እኔ ያልገለጽኩት፡፡
ካንቺ የሰረፀ ያ  ኃያሉ ፍቅርሽ ፤
ከየት ቋንቋ ላምጣ እንደምን ልግለጽሽ፡፡
እማ… እማዬ… እኔ ብቻ ሳልሆን እኔን የሚመስሉ፤
ሰው ሁነው ተፈጥረው በዓለም ዙሪያ ያሉ ፤
ስለእናት አዚመው ስለእናት ቢቀኙ፤
ዓለምን ቢዞሩ ገላጭ ቃል ቢያገኙ፤
አልሆነላቸውም ምንም ቢባዝኑ ፤
ምንም ቢፈትሹ የትም ቢኳትኑ፡፡
ስለዚህም መግለጫ ቃል ቢያጡ፤
በአንደነት በጋራ ዓለሜ ናት ብለው ለአንቺ ስም አወጡ፡፡
እኔስ የእኔ እናት፣ ውዴ የእኔ ሕይወት፣ ስላንቺ ምንም አልልም፤
ከቶም አልጽፍልሽም፤ ዝምታ እንጂ አንቺን ቃላት አይገልጽሽም፤
ስለአንቺ አላወራም አልዘምርልሽም፤
ፈጣሪ ሲፈጥርሽ አልፈጠረልሽም፤
በምድር የሚገኝ ገላጭ ቃል የለሽም፡፡

No comments:

Post a Comment