Saturday, February 4, 2012

ለክርስቶስ የቀረበ የምስጋና ቅኔ(ከሶርያ ቅዱሳን አባቶች)

(ማኀልየ ማኅልይ ዘሶርያ)
ትርጉም በዲ/ን ሽመልስ መርጊያ
26/05/2004

ከማር እንጀራ የማር ወለላ እንዲንጠባጠብ፤
ለልጅዋ ፍጹም ፍቅር ካላት እናት ጡት ወተቱ ሞልቶ አንዲፈስ፤
አምላኬ ሆይ ከአንተ ዘንድ የእኔ ናፍቆት ይህ ነው፡፡
የፏፏቴው ውኃ ድምፅ እያሰማ እንደሚወርድ፤
እንዲሁ ልቤ እንደ ፏፏቴ ለጌታዬ ምስጋናውን አፈሰሰ፤
ከንፈሮቼም ውዳሴህን አፈለቁ፡፡
አንደበቴም ከእርሱ ጋር በመነጋገሩ ጣፈጠ፤
ጉልበቶቼም ለእርሱ ባቀረብኩት ዝማሬ ጸኑ፤
ከእርሱ ባገኘሁት ታላቅ ደስታ ፊቴ  ፈካ፤
መንፈሴም እርሱ ለእኔ ባለው ፍቅር ሐሴትን አደረገ፤
በእርሱም ነፍሴ እንደ ፀሐይ ደምቃ አበራች፡፡
ጌታን የሚያከበርና የሚፈራ ሰው እርሱ ብርቱ ሰው ነው፤
መዳኑ የታወቀና የተረጋገጠ ነው፡፡
እርሱ ዘለዓለማዊ ሕይወትን ያገኛል፤
በእርሱ አምኖ በምግባር ለመሰለው ሕይወትን ይሰጠዋል፤
ሃሌ ሉያ !!
አባታችን ሆይ በሰማይ የምትኖር…..

No comments:

Post a Comment