Sunday, January 15, 2012

ኦ ክርሰቶስ!!!


ትርጉም በዲ/ን ሽመልስ
05/04/2004 ዓ.ም
አዲስ አበባ
ኦ ክርስቶስ ስላንተ ሴቶች ወንዶችን ተከትለው ሄዱ፡፡(ሰው አባትና እናቱን ይተዋል ከሚስቱም ጋር ይጣበቃል የሚለውን ቃል ሽረው) ዘፍ.2፡24 ፡፡መበለት የነበረችው ትዕማር እርሱን(የባሎቿን አባት የአባታችን የያዕቆብ ልጅ ይሁዳን) ተመኘችው ፡፡ሩት ስለአንተ በእድሜ ያረጀውን ሰው ወደደችው፡፡ አዎን ሰዎችን በዝሙቷ የምትማርከው ረዓብ ባንተ ተማረከች፡፡ ትዕማር ጨለማን ለብሳ በጨለማ ወጣች ብርሃንንም ሰረቀች፡፡ ንጹሕ ባልሆነ መንገድ ንጹሕ የሆነውን ሰረቀች፡፡ ሰውነቷን በማራቆት አንተን ለመስረቅ ተጓዘች፡፡ንጹሕ ካልሆነው ንጹሕ የሆነውን የምታስገኝ አምላካችን ሆይ! ሰይጣን እርሷን አይቶ ተንቀጠቀጠ፤እናም እርሷን ለማሸበር ተፋጠነ፤ በእርሷ አእምሮ ውስጥ ፍርድን አስገባ፤ ነገር ግን እርሷ አልተሸበረችም፡፡ ስለአንተ በድንጋይ መወገርና በሰይፍ መቀላት አላስደነገጣትም፡፡ ይሁዳን ለማጥመድ ዘማውያንን መሰለች ከእዛ በኋላ ግን ልትዘሙት አልወጣችም፤ ምክንያቱም ዝሙትን የማይፈቅደውን ጌታ ሽታ ነውና የወጣችው፡፡ (ቅ/ ኤፍሬም ዘሶሪያ)

1 comment:

  1. This comment has been removed by a blog administrator.

    ReplyDelete