Sunday, January 15, 2012

ኤደን ገነት በቅዱስ ይስሐቅ ሶርያዊ

“ኤደን ገነት የተባለችው የእግዚአብሔር ፍቅር ናት፡፡ በዚች ውስጥ የገነት በረከቶች ሁሉ ይገኛሉ፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ከምድር በመነጠቅ መለኮታዊ ምግብን ተመግቦ የጠገበባት ቦታ ይህቺ ናት፡፡(፪ቆሮ.፲፪፥፪-፬) ከዚያ የሕይወት ዛፍ ፍሬ በልቶ ከጠገበ በኋላ “ዐይን ያላየችው ጆሮም ያለሰማው በሰው ልቡና ያልታሰበው እግዚአብሔር ለሚወዱት ያዘጋጀው” ብሎ መሰከረላት፡፡( ፩ቆሮ.፪፥፱ )… እንደእኔ እምነት በሲኦል ያሉ ነፍሳት የሚቀጡት በፍቅር ማጣት ነው እላለሁ ፡፡ ፍቅርን ከማጣት የበለጠ እጅግ የሚጎዳና የሚያም ሕመም ምን አለ ? በፍቅር ላይ በደልን የፈጸሙ ሰዎች በራሳቸው ላይ እጅግ የከበደና አስፈሪ ቅጣትን አመጡ ፡፡….” (ቅዱስ ይስሐቅ)

No comments:

Post a Comment